ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ: ሰኔ 25/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይግለጡ አብዛ ገለፁ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመቀናጀት በየደረጃው ለሚገኙ የፓርቲ አመራሮች ያዘጋጀው የስልጠና መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይግለጡ አብዛ እንደገለፁት ለህብረተሰቡ አስፈላጊውን አገልግሎት በተገቢ ሁኔታ መስጠት እንዲቻልና የፖለቲካ ስራዎችም በአደረጃጀት እንዲተገበሩ በየደረጃው የሚገኙ ሁሉም የፓርቲ አመራሮች ወጥ አሰራሮችን ሊከተሉ ይገባል።
ስራዎች በመመሪያና ደንብ መመራት አለባቸው ያሉት አቶ ይግለጡ በዛሬው ዕለት ከ13 በላይ መምሪያዎች ላይ ለፓርቲ አመራሮቹ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል።
አመራሩ የተሻለ ግንዛቤ ይዞ ህብረተሰቡን በተገቢ ሁኔታ ማገልገል እንደሚገባ ጠቁመው እንደ ሀገር የተጀመሩ የልማት ውጥኖችን ከግብ ማድረስ እንዲቻልና በዚሁም የሀገሪቱ ሁለንተናዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ በቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ አመላክተዋል።
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ከሰራን ችግሮቻችንን መፍታት እንችላለን ያሉት አቶ ይግለጡ ለሁለንተናዊ የኢትዮጵያ ብልጽግና ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ያነጋገርናቸው የስልጠናው ተሳታፊዎችም በበኩላቸው ስልጠናው ለተቋም ግንባታ ብሎም ለአመራር ግንባታ ፈይዳው የጎላ መሆኑን ጠቁመው በያካባቢያቸው ዓላማውን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ አመላክተዋል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ