የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ ሁለተኛ ቀን ውሎ መካሄድ ጀምሯል
ሀዋሳ: ሰኔ 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሠላም፣ አንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ ሁለተኛ ቀን ውሎ የዕለቱ የክብር እንግዳ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ፥ በክልሉ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ታስቦ መዘጋጀቱ ተጠቁሟል።
መድረክ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ በየደረጃው ከሚገኙ መዋቅሮች የተወጣጡ የክልሉ ተወላጅ ምሁራንና ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸዉ።
“ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ በሚገኘው ኮንፈረንስ በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ከ 1 ሺ በላይ ተሳታፊዎች በመካፈል ላይ ናቸዉ።
ኮንፈረንሱ በሁለተኛ ቀን ዉሎዉ የክልሉን አንድነት የሚያጠናክሩ ተቋማዊ አደረጃጀቶችና ፎረሞች ምስረታን ጨምሮ በቀሪ ጉዳዮች ላይ በመምከር ዉሳኔዎች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
የወባ በሽታ ስርጭትን የመከላከልና የመቆጣጠርን ጉዳይ ቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ
አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ተገልጋዩን ለማርካት እየሰራ መሆኑን የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ
የባስኬቶ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 10ኛ አመት የሥራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን አካሂዷል