የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ ሁለተኛ ቀን ውሎ መካሄድ ጀምሯል
ሀዋሳ: ሰኔ 24/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሠላም፣ አንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ ሁለተኛ ቀን ውሎ የዕለቱ የክብር እንግዳ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ኮንፈረንስ፥ በክልሉ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ታስቦ መዘጋጀቱ ተጠቁሟል።
መድረክ የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ በየደረጃው ከሚገኙ መዋቅሮች የተወጣጡ የክልሉ ተወላጅ ምሁራንና ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ናቸዉ።
“ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ በሚገኘው ኮንፈረንስ በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ከ 1 ሺ በላይ ተሳታፊዎች በመካፈል ላይ ናቸዉ።
ኮንፈረንሱ በሁለተኛ ቀን ዉሎዉ የክልሉን አንድነት የሚያጠናክሩ ተቋማዊ አደረጃጀቶችና ፎረሞች ምስረታን ጨምሮ በቀሪ ጉዳዮች ላይ በመምከር ዉሳኔዎች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ