የህብረት ስራ ማህበራት ለግብርና ምርትና ምርታማነት የሚያበረክቱት አስታዋጾ ከፍተኛ በመሆኑ አውቆ ትኩረት ስጥቶ ሊሰሩ እንደሚገባ የማዕከላዊ እትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ ከምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለቅመማ ቅመም ምርት ዘላቂ የገበያ ትስስር ለመፈጠር ከአምራች ህብረት ስራ ማህበራትና ኢንተርፕራይዝ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ መድረክ በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በክልሉ በተበታተነ መልኩ እየለማ የሚገኘው የሮዝመሪ ምርት በህብረት ስራ ማህበራት በስፋት እየለማ በመሆኑ ክልሉና ሀገሪቱ ከዘርፉ መግኘት የሚገባቸውን ጥቅም በማግኘት ላይ እንደሆነ ነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የግብርና እና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር የተናገሩት።
በዚህ ዘርፍ የታየው ውጤታማነት በሌሎችም በግብርና መስክ የተሻለ ምርትና ምርታማነትን አምርቶ ለዓለም ገበያ በስፋትና በጥራት ለማምራት የህብረት ስራ ማህበራት አውቆ ማምራት አስፈላጊ መሆኑን ነው ኃላፊው የገለጹት።
በመድረኩ ለይ ከጉራጌ፣ከምስራቅ ጉራጌ፣ከስልጤ እና ከየም ዞኖች የህብረት ስራ አመራሮች እና የሮዝመሪ አምራች አ/አደሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አብዱልሀፊዝ መሀመድ

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ