የህብረት ስራ ማህበራት ለግብርና ምርትና ምርታማነት የሚያበረክቱት አስታዋጾ ከፍተኛ በመሆኑ አውቆ ትኩረት ስጥቶ ሊሰሩ እንደሚገባ የማዕከላዊ እትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ ከምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለቅመማ ቅመም ምርት ዘላቂ የገበያ ትስስር ለመፈጠር ከአምራች ህብረት ስራ ማህበራትና ኢንተርፕራይዝ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ መድረክ በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በክልሉ በተበታተነ መልኩ እየለማ የሚገኘው የሮዝመሪ ምርት በህብረት ስራ ማህበራት በስፋት እየለማ በመሆኑ ክልሉና ሀገሪቱ ከዘርፉ መግኘት የሚገባቸውን ጥቅም በማግኘት ላይ እንደሆነ ነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የግብርና እና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር የተናገሩት።
በዚህ ዘርፍ የታየው ውጤታማነት በሌሎችም በግብርና መስክ የተሻለ ምርትና ምርታማነትን አምርቶ ለዓለም ገበያ በስፋትና በጥራት ለማምራት የህብረት ስራ ማህበራት አውቆ ማምራት አስፈላጊ መሆኑን ነው ኃላፊው የገለጹት።
በመድረኩ ለይ ከጉራጌ፣ከምስራቅ ጉራጌ፣ከስልጤ እና ከየም ዞኖች የህብረት ስራ አመራሮች እና የሮዝመሪ አምራች አ/አደሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አብዱልሀፊዝ መሀመድ

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ