የህብረት ስራ ማህበራት ለግብርና ምርትና ምርታማነት የሚያበረክቱት አስታዋጾ ከፍተኛ በመሆኑ አውቆ ትኩረት ስጥቶ ሊሰሩ እንደሚገባ የማዕከላዊ እትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረት ስራ ልማት ኤጀንሲ ከምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለቅመማ ቅመም ምርት ዘላቂ የገበያ ትስስር ለመፈጠር ከአምራች ህብረት ስራ ማህበራትና ኢንተርፕራይዝ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ጋር የግንዛቤ መድረክ በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በክልሉ በተበታተነ መልኩ እየለማ የሚገኘው የሮዝመሪ ምርት በህብረት ስራ ማህበራት በስፋት እየለማ በመሆኑ ክልሉና ሀገሪቱ ከዘርፉ መግኘት የሚገባቸውን ጥቅም በማግኘት ላይ እንደሆነ ነው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የግብርና እና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር የተናገሩት።
በዚህ ዘርፍ የታየው ውጤታማነት በሌሎችም በግብርና መስክ የተሻለ ምርትና ምርታማነትን አምርቶ ለዓለም ገበያ በስፋትና በጥራት ለማምራት የህብረት ስራ ማህበራት አውቆ ማምራት አስፈላጊ መሆኑን ነው ኃላፊው የገለጹት።
በመድረኩ ለይ ከጉራጌ፣ከምስራቅ ጉራጌ፣ከስልጤ እና ከየም ዞኖች የህብረት ስራ አመራሮች እና የሮዝመሪ አምራች አ/አደሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አብዱልሀፊዝ መሀመድ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል