የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በወረዳው 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ማድረጉን በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ግብርና፣ አከባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካሣሁን ዳዒሞ ገልጸዋል።
በበልግና በምኸር ወቅቶች ለመትከል ከታቀደው 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ችግኞች በበልግ ተከላ 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ችግኞች ተተክለው መጠናቀቁን ተከትሎ በምኸር ወቅት ተከላ የተቀረውን 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል አቶ ካሣሁን ።
በወረዳው በበልግ ወቅት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በፍራፍሬ ችግኞች ላይ ትኩረት መደረጉን ያነሱት ኃላፊው በቀጣይም ዘርፈ-ብዙ ጥቅም ባላቸው ችግኞች ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ኃላፊው አብራርተዋል ።
በአመያ ዙሪያ ወረዳ ውስጥ 41 የችግኝ ጣቢያዎች መኖራቸውን በመጠቆም በነዚህ ሁሉም ጣቢያዎች ችግኞቹን ለተከላ ዝግጁ የማድረግ ሥራ ተሰርቷል ብለዋል ።
ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞችም በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን በመጥቀስ የጽድቀት መጠናቸውም ከ 90 በ መቶ በላይ ስለመሆኑም ነው አቶ ካሣሁን የተናገሩት ።
በወረዳው ከሚገኙ ግብርና ባለሙያዎች መካከልም አቶ ሙሉዓለም ወዳጄ እና አቶ ዘውዴ ሾጋሞ በበኩላቸው ለመርሃ-ግብሩ በችግኝ ጣቢያዎቻቸው ችግኞችንና ጉድጓዶችን ለተከላ ዝግጁ የማድረግ ስራ መጠናቀቁን ገልፀዋል ።
በችግኝ ጣቢያዎች የስራ ዕድሉ ተጠቃሚ የሆኑ ግለሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጠቃሚነታቸው እያደገ ስለመሆኑ ተናግረዋል ።
ዘጋቢ ፡ ደረጀ ተፈራ ከዋካ ጣቢያ

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ