በአካባቢው ዘላቂነት ያለው ሠላምና ልማት እንዲረጋገጥ የሸኮና አካባቢው ምሁራን ጥናትና ምርምር ማህበር እያበረከተ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን የማህበሩ አባላትና ደጋፊዎች ተናገሩ
የሸኮ እና አከባቢዉ ምሁራን ጥናትና ምርምር ማህበር የ2017 ዓ/ም በጀት አመት ማጠቃለያ ጉባኤዉን በሸካ ዞን በቴፒ ከተማ አካሂዷል።
በጉባኤው ላይ የተሳተፉ የማህበሩ አባላቶችና ደጋፊዎች በሰጡት ሀሳብና አስተያየት በአካባቢው ዘላቂነት ያለው ሠላምና ልማት እንዲረጋገጥ የሸኮና አካባቢው ምሁራን ጥናትና ምርምር ማህበር እያበረከተ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
የምሁራን ማህበሩ ባለፉት ጥቂት አመታት ብሔረሰቡ ዘንድ የሚታዩ የልማት ችግሮች በቅርበት እንዲፈቱ የጥናትና ምርምር ስራዎችን በቅርበት በመስራት የላቀ ሚና መጫወቱንም አንስተዋል
በቀጣይም የሸኮ ብሄረሰብ ባህል ታሪክ ወግ እንዲሁም የቋንቋ ልማት ላይ ከሌሎችን ወንድም ህዝቦች ጋር ያለውን አብሮነትና አንድነት ይበልጥ እንዲጠናከር የምሁራን ማህበሩ የተጠናከረ ስራ መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል።
የማህበሩ የበላይ ጠባቂና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በጉባኤው ማጠቃለያ ንግግራቸው የማህበሩ አባላቶችና ምሁራን በአካባቢው ዘላቂነት ያለው ሠላምና ልማት እንዲረጋገጥ አበክረው መስራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ማህበሩ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ባለፉት አመታት የብሔሩን አንድነት ከማጠናከር ጀምሮ በአካባቢው ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ እንዲሁም በህዝቦች መካከል ያለው አብሮነት እንዲጠናከር የሰራቸው ስራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል።
በዕለቱ የሚዛን ቴፒ ዩንቨርስቲ መምህርና የማህበሩ ስራ አስኪያጅ የሆኑት መምህር ኢህአዴግ ገዳ ማህበሩ በ2017 ዓ.ም በጀት አመት ያከናወናቸውን ስራዎች በጥንካሬና በድክመት ያጋጠሙ ችግሮች ዝርዝር ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
በጉባኤው ላይ ከፌደራል ከክልል ከዞንና ከወረዳ የተውጣጡ የተለያዩ አመራሮች እና የሀገርሽማግሌዎችና የምሁራን ማህበሩ አባላቶች ተሳታፊዎች ሆነዋል።
ዘጋቢ :ጦያር ይማም -ከሚዛን ቅርንጫፍ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል