በሣውላ ከተማ የሚገኘው የወንባ ወንዝ ብረት ድልድይ በሶዶ ዲንኬ ሣውላ ሸፊቴ መንገድ ስራ ምክንያት መነሳቱን ተከትሎ በህብረተሰቡ ላይ የተፈጠረውን እንግልት ለመቀነስ የተለዋጭ መንገድ ስራ በመጠናቀቅ ላይ ነው።
የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ የድልድዩን ስራ በጎበኙበት ወቅት እንዳሉት በወንባ ወንዝ ድልድይ ላይ የሚደረገው እንቅስቃሴ በመቋረጡና ተለዋጭ መንገድ ባለመኖሩ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ በመፈጠሩና ህብረተሰቡም ላልተፈለገ እንግልት መዳረጉን ተከትሎ ክረምት ከመግባቱ አስቀድሞ የብረት ድልድይ የመግጠም ስራ እየተሰራ ይገኛል።
በወንዙ ላይ ተለዋጭ ድልድይ መሰራቱ አነስተኛና መካከለኛ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ህብረተሰቡ በእግሩ ለመንቀሳቀስም ጭምር መፍትሔ መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው አንስተዋል።
ይህን ተከትሎ በአካባቢው የተፈጠረውን ውጣ ውረድ ለማስቀረት የግንባታ ሂደቱ ተጠናቆ ብረት የመገጣጠም ስራ ብቻ መቅረቱን ጠቅሰው የመግጠሙን ስራ በአንድ ሳምንት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ