በሣውላ ከተማ የሚገኘው የወንባ ወንዝ ብረት ድልድይ በሶዶ ዲንኬ ሣውላ ሸፊቴ መንገድ ስራ ምክንያት መነሳቱን ተከትሎ በህብረተሰቡ ላይ የተፈጠረውን እንግልት ለመቀነስ የተለዋጭ መንገድ ስራ በመጠናቀቅ ላይ ነው።
የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ የድልድዩን ስራ በጎበኙበት ወቅት እንዳሉት በወንባ ወንዝ ድልድይ ላይ የሚደረገው እንቅስቃሴ በመቋረጡና ተለዋጭ መንገድ ባለመኖሩ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ በመፈጠሩና ህብረተሰቡም ላልተፈለገ እንግልት መዳረጉን ተከትሎ ክረምት ከመግባቱ አስቀድሞ የብረት ድልድይ የመግጠም ስራ እየተሰራ ይገኛል።
በወንዙ ላይ ተለዋጭ ድልድይ መሰራቱ አነስተኛና መካከለኛ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ህብረተሰቡ በእግሩ ለመንቀሳቀስም ጭምር መፍትሔ መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው አንስተዋል።
ይህን ተከትሎ በአካባቢው የተፈጠረውን ውጣ ውረድ ለማስቀረት የግንባታ ሂደቱ ተጠናቆ ብረት የመገጣጠም ስራ ብቻ መቅረቱን ጠቅሰው የመግጠሙን ስራ በአንድ ሳምንት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አይናለም ሰለሞን – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ