በከተማው የተፈጠረውን ምቹ አጋጣሚ ተጠቅመው እየሠሩ እንደሚገኝ በዘርፉ የተሰማሩ አልሚዎች ተናግረዋል።
ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት የባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፎረም በማቋቋም እየሠሩ እንደሚገኝ የገለጹት የይርጋጨፌ ከተማ ከንቲባ አቶ ታደለ ጥላሁን፤ ለኢንቨስትመንት ዋነኛ ጉዳይ የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋነትና ከቢሮክራሲ የጸዳ ማድረግ ነው ብለዋል።
የሚሠሩ ግንባታዎችን ኮሚቴ አዋቅረው ታች በመውረድ የድጋፍና ክትትል ሥራዎች እየተሠሩ እንዳሉም ተናግረዋል።
በኢንቨስትመንቱ መስክ መሰማራት የሚፈልግ ማንኛውም ባለሀብት አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍ እንደሚደረግ የገለጹት ከንቲባው፤ በኢንቨስትመንቱ ከተማዋን ከማልማት ባለፈ ለራስ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጠይቀዋል።
የይርጋጨፌ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ታምራት፤ በከተማዋ ከሠላሳ በላይ ኢንቨስተሮች በግንባታው ተሰማርተው እያለሙ መሆናቸውን ጠቅሰው ሌሎችም ሲመጡ በተገቢው ማስተናገድ እንደሚገባና ኢንቨስትመንቱ ሙሉ እንዲሆን የጌጠኛ ድንጋይ፣ የኮሪደርና የአረንጓዴ ስፍራዎች ልማት እየተሠሩ እንዳሉ ገልጸዋል።
አቶ ዮሴፍ ኡዶ፣ ኤርሚያስ ሌሲዎንና ሌሎችም በሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ በሆቴል፣ በሞቴልና የኤክትሪክ መኪና ቻርጅ ማድረጊያ የተሰማሩና በሂደት ላይ ያሉ አልሚዎች ናቸው። በከተማዋ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የታየው የኢንቨስትመንት መነቃቃት ይበል የሚያሰኝ እንደሆነም አስረድተዋል።
ዘጋቢ: ውብሸት ካሣሁን – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ23ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛና በማታ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 347 ተማሪዎችን አስመረቀ
በ2018 በጀት ዓመት የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል – አቶ ፍቅሬ አማን
ሚዲያን ለአዎንታዊ ነገር በመጠቀም ወጣቱ ሀገርን መገንባት አለበት – የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን