በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ አጀንዳ ለማሰባሰብ የተወካዮች ልየታ ላይ ያለመ መድረክ መካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 01/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ አጀንዳ ለማሰባሰብ የተወካዮች ምልመላ ላይ ያለመ መድረክ በሀዋሳ መካሄድ ጀምሯል፡፡
በመድረኩ ከተለያዩ የህብረተሰብ አደረጃጀቶች የተውጣጡ አባላትት ተሳታፊ እየሆኑ ነው።
እራሳቸውን የሚገልፁበት ዋና መተዳደሪያ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ዕድሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ መምህራን፣ የተገለሉ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ እንዲሁም ተፈናቃዮችን በአጀንዳ ቀረፃ ምክክር መድረክ ላይ ለማሳተፍ እየሰራ መሆኑን ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ
More Stories
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ
“የብልጽግና ጉዞአችንና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ክልላዊ የንግዱ ማሕበረሰብ ማጠቃለያ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው
በዞኑ ኩረጃን የሚፀየፍ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ