በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ አጀንዳ ለማሰባሰብ የተወካዮች ልየታ ላይ ያለመ መድረክ መካሄድ ጀመረ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 01/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ አጀንዳ ለማሰባሰብ የተወካዮች ምልመላ ላይ ያለመ መድረክ በሀዋሳ መካሄድ ጀምሯል፡፡
በመድረኩ ከተለያዩ የህብረተሰብ አደረጃጀቶች የተውጣጡ አባላትት ተሳታፊ እየሆኑ ነው።
እራሳቸውን የሚገልፁበት ዋና መተዳደሪያ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ዕድሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ መምህራን፣ የተገለሉ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ እንዲሁም ተፈናቃዮችን በአጀንዳ ቀረፃ ምክክር መድረክ ላይ ለማሳተፍ እየሰራ መሆኑን ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ዘጋቢ፡ ጀማል የሱፍ

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ