የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ጋር የቱሪስት አገልግሎት ብቃት ማረጋገጫ አሰጣጥ ላይ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ይገኛል::
ክልሉ በሆቴል ኢንቨስትመንት ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል ያሉት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኑሪ ከድር ዘርፉን የሚቀላቀሉ አዳዲስ ሆቴሎች በመኖራቸው ብቃታቸውን ማረጋገጥ አስፈልጓል ነው ያሉት።
ይህ መድረክ የብቃት ማረጋገጡን ስራ ከንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ጋር በቅንጅት መስራትን ያለመ መሆኑ ምክትል ኃላፊው ጠቁመዋል።
ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት የሚሰጡና በኮከብ ደረጃ የሚመደቡ ሆቴሎች እንዲበዙ ለሚሰሩ ስራዎች ቢሮው ድጋፍና ክትትል ያደርጋል ተብሏል።
የሆቴል አገልግሎት ሰጪ ተቋም ብቃት እንዲረጋገጥ የሚያስችል ስራ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሲሰራ የንግድ ስርዓቱ ህጋዊ እንዲሆን ያስችላል ያሉት የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ምክትል ቢሮ ሃላፊ ቀመሪያ ረሻድ ይሄም የሁለቱን ቢሮዎች ቅንጅታዊ አሰራር አስፈላጊነት ያሳያል ብለዋል ::
በመድረኩ በሆቴልና ቱሪዝም አገልግሎት ዘርፍ
የነበሩ ጉድለቶችን በማረም የሆቴል ኢንቨስትመት ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።
ዘጋቢ:ሲሳይ ደበበ

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ