በዳውሮ ዞን ሎማ ቦሣ ወረዳ ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ነፍሰጡር እናቶች ድጋፍ ተደረገ
ድጋፉ በኢፌዴሪ ግብርና ሚኒስቴር ፣ ጤና ሚኒስቴር እና በክልሉ ግብርና ቢሮ ማቺንግ ፈንድ ሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮግራም ጋር በመተባበር እንደሆነም ተጠቁሟል
በዞኑ ሎማ ቦሳ ወረዳ ግብርና አከባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽ/ቤት ከሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነት በተገኘው ገንዘብ ድጋፍ ከቦሳ ሾጋ፣ ቦሳ ፀደፋ፣ ቱላማ ጣማ እና ከኤላ ባቾ ቀበሌያት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ 55 አጥቢና ነፍሰ ጡር እናቶች ድጋፍ አድርጓል።
በሰቆጣ ቃልኪዳን የሚከናወኑ ተግባራት በወረዳው የህጻናትን የመቀንጨር ምጣኔ ለመቀነስ ጉልህ አስተዋጽኦ እየተወጣ እንደሚገኝ የተናገሩት የፕሮግራሙ አስተባባሪ አቶ አስፋው ቦሎላ ናቸው ።
እንደ በአስተባባሪው ገለጻ ህብረተሰቡ ቤት ያፈራዉን በአግባቡ አዘጋጅቶ እንዲመገብ፣ ከኋላቀር የልጆች አስተዳደግ ባህልና ልምድ እንዲላቀቅ ፣ እናት በእርግዝና ወቅት በቂ ምግብ እንድትመገብ ፤ ከወልድም በኋላ ጡት በበቂ መጠን እንድታጠባ እና ከ6 ወር በኋላ ተጨማሪ ምግብን ህፃኑ እንዲጀምር የግንዛቤ ማስጨበጭያ ስልጠና መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
የጨቅላ ህፃናትን መቀንጨር ለመከላከል እና በዚህም ሳቢያ ሊመጣ የሚችለውን ሞት ለመቀነስ የወተት ላም ፣ በግና ፍየል ግዢ በመፈጸም ስርጭት እያደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
ድጋፍ የተደረገላቸው እናቶችም በበኩላቸው፣ ለተደረገላቸው ድጋፍ አመሰግነው በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት ተግተው እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
ዘጋቢ ፡ አሸናፊ ግዛው – ዋካ ጣቢያችን
በዳውሮ ዞን ሎማ ቦሣ ወረዳ ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ነፍሰጡር እናቶች ድጋፍ ተደረገ

More Stories
የቡርጂ ዞን ምክር ቤት አቶ ትንሳኤ ዮሐንስ ወጌ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ ሾመ
የወባ በሽታ ስርጭትን የመከላከልና የመቆጣጠርን ጉዳይ ቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ
አገልግሎት አሰጣጡን በማዘመን ተገልጋዩን ለማርካት እየሰራ መሆኑን የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ