በዳውሮ ዞን ሎማ ቦሣ ወረዳ ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ነፍሰጡር እናቶች ድጋፍ ተደረገ
ድጋፉ በኢፌዴሪ ግብርና ሚኒስቴር ፣ ጤና ሚኒስቴር እና በክልሉ ግብርና ቢሮ ማቺንግ ፈንድ ሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮግራም ጋር በመተባበር እንደሆነም ተጠቁሟል
በዞኑ ሎማ ቦሳ ወረዳ ግብርና አከባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት ጽ/ቤት ከሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነት በተገኘው ገንዘብ ድጋፍ ከቦሳ ሾጋ፣ ቦሳ ፀደፋ፣ ቱላማ ጣማ እና ከኤላ ባቾ ቀበሌያት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ 55 አጥቢና ነፍሰ ጡር እናቶች ድጋፍ አድርጓል።
በሰቆጣ ቃልኪዳን የሚከናወኑ ተግባራት በወረዳው የህጻናትን የመቀንጨር ምጣኔ ለመቀነስ ጉልህ አስተዋጽኦ እየተወጣ እንደሚገኝ የተናገሩት የፕሮግራሙ አስተባባሪ አቶ አስፋው ቦሎላ ናቸው ።
እንደ በአስተባባሪው ገለጻ ህብረተሰቡ ቤት ያፈራዉን በአግባቡ አዘጋጅቶ እንዲመገብ፣ ከኋላቀር የልጆች አስተዳደግ ባህልና ልምድ እንዲላቀቅ ፣ እናት በእርግዝና ወቅት በቂ ምግብ እንድትመገብ ፤ ከወልድም በኋላ ጡት በበቂ መጠን እንድታጠባ እና ከ6 ወር በኋላ ተጨማሪ ምግብን ህፃኑ እንዲጀምር የግንዛቤ ማስጨበጭያ ስልጠና መሰጠቱን ጠቅሰዋል።
የጨቅላ ህፃናትን መቀንጨር ለመከላከል እና በዚህም ሳቢያ ሊመጣ የሚችለውን ሞት ለመቀነስ የወተት ላም ፣ በግና ፍየል ግዢ በመፈጸም ስርጭት እያደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
ድጋፍ የተደረገላቸው እናቶችም በበኩላቸው፣ ለተደረገላቸው ድጋፍ አመሰግነው በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት ተግተው እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
ዘጋቢ ፡ አሸናፊ ግዛው – ዋካ ጣቢያችን
በዳውሮ ዞን ሎማ ቦሣ ወረዳ ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ ነፍሰጡር እናቶች ድጋፍ ተደረገ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል