የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ፍትሃዊ አገልግሎት ለማህበረሰቡ መስጠት ላይ ትኩረት አድርገው መስራት አለባቸው – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚንቀሳቀሱ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ የጋራ ፎረም ተካሂዷል
በዚህ ወቅት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ባስተላለፉት መልዕክት የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት የማህበረሰብ ለውጥ እንዲመጣ የራሳቸውን ሚና እየተወጡ እንደሚገኙ ጠቅሰው ይህንን ተግባር አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።
በክልሉ ሁሉም አከባቢዎች ስራዎች በፍትሃዊነት ተደራሽ እንዲሆን ጥረት ማድረግ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል፡፡
ዕኩል እድል የተሰጣቸው አከባቢዎች የማስፈፀም አቅማቸውን አሟጦ በመጠቀም የሚፈለገው ለውጥ እንዲመጣ ርብርብ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ነው ያሉት
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዘጠና ዘጠኝ ሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች 8ቢሊየን ብር ካፒታል በማስመዝገብ በተለያዩ ዘርፎች የልማት ስራዎች አየሰሩ ይገኛሉ።
በፎረሙ በክልሉ ሁለንተናዊ ለውጥ ላይ የራሳቸውን አሻራ ላስቀመጡ ሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው የእውቅና ሰርተፊኬት አበርክተዋል።
ዘጋቢ :ሲሳይ ደበበ

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ