በወላይታ ሶዶ ከተማ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ
ዛሬ ከቀኑ ከ7:20 ኮድ (3)63419 ET የተሰኘ የፍሳሽ ማስወገጃ ተሽከርካሪ ባደረሰው የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሶዶ ከተማ ፖሊሲ ዋና አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገልፀዋል።
የአደጋው መንስኤ በጉዞ ላይ የነበረ ፍሳሽ ማስወገጃ መኪና ባገጠመው የቴክኒክ ችግር ሳቢያ ፍሬን አልታዘዝ ብሎት አደጋው መድረሱን ምክትል ኮማንደር ጠቁመዋል ።
በአደጋው ለህልፈት የተዳረጉት ሁለቱ በመንገድ ላይ የነበሩ የሌላ ተሸከርካሪ ረዳቶችና አንድ የሊስትሮ ባለሙያ
መሆኑን ታውቋል። ከባድ አደጋ የደረሰባቸው 3 ሰዎችም የህክምና እርዳታ እያገኙ ነው ፡፡
አደጋ አድራሹ ተሽከርካሪ መንገድ ዳር በነበሩ 6 ተሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ የንብረት ጉዳት ማድረሱን ምክትል ኮማንድሩ ተናግረዋል ፡፡
ዘጋቢ ፡ በቀለች ጌቾ
More Stories
የአካባቢ ብክለትን በዘላቂነት በመከላከል የተሻለች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የተገኘውን የሀይማኖት ነፃነት ማስቀጠል የሁሉም ድርሻ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የኡለማ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ ሸክ መሀመድ ዘይን ዘይረዲን ተናገሩ
የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ፍትሃዊ አገልግሎት ለማህበረሰቡ መስጠት ላይ ትኩረት አድርገው መስራት አለባቸው – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)