በወላይታ ሶዶ ከተማ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ
ዛሬ ከቀኑ ከ7:20 ኮድ (3)63419 ET የተሰኘ የፍሳሽ ማስወገጃ ተሽከርካሪ ባደረሰው የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሶዶ ከተማ ፖሊሲ ዋና አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገልፀዋል።
የአደጋው መንስኤ በጉዞ ላይ የነበረ ፍሳሽ ማስወገጃ መኪና ባገጠመው የቴክኒክ ችግር ሳቢያ ፍሬን አልታዘዝ ብሎት አደጋው መድረሱን ምክትል ኮማንደር ጠቁመዋል ።
በአደጋው ለህልፈት የተዳረጉት ሁለቱ በመንገድ ላይ የነበሩ የሌላ ተሸከርካሪ ረዳቶችና አንድ የሊስትሮ ባለሙያ
መሆኑን ታውቋል። ከባድ አደጋ የደረሰባቸው 3 ሰዎችም የህክምና እርዳታ እያገኙ ነው ፡፡
አደጋ አድራሹ ተሽከርካሪ መንገድ ዳር በነበሩ 6 ተሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ የንብረት ጉዳት ማድረሱን ምክትል ኮማንድሩ ተናግረዋል ፡፡
ዘጋቢ ፡ በቀለች ጌቾ
More Stories
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የእምርታ ቀንን በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት:-
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) መልዕክት፡-