በወላይታ ሶዶ ከተማ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ
ዛሬ ከቀኑ ከ7:20 ኮድ (3)63419 ET የተሰኘ የፍሳሽ ማስወገጃ ተሽከርካሪ ባደረሰው የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሶዶ ከተማ ፖሊሲ ዋና አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገልፀዋል።
የአደጋው መንስኤ በጉዞ ላይ የነበረ ፍሳሽ ማስወገጃ መኪና ባገጠመው የቴክኒክ ችግር ሳቢያ ፍሬን አልታዘዝ ብሎት አደጋው መድረሱን ምክትል ኮማንደር ጠቁመዋል ።
በአደጋው ለህልፈት የተዳረጉት ሁለቱ በመንገድ ላይ የነበሩ የሌላ ተሸከርካሪ ረዳቶችና አንድ የሊስትሮ ባለሙያ
መሆኑን ታውቋል። ከባድ አደጋ የደረሰባቸው 3 ሰዎችም የህክምና እርዳታ እያገኙ ነው ፡፡
አደጋ አድራሹ ተሽከርካሪ መንገድ ዳር በነበሩ 6 ተሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ የንብረት ጉዳት ማድረሱን ምክትል ኮማንድሩ ተናግረዋል ፡፡
ዘጋቢ ፡ በቀለች ጌቾ

More Stories
ህዝቡ የሚያነሳቸውን የፍትህ ጥያቄዎች በአግባቡ ከመመለስ አኳያ የፍትህ ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ አሳሰቡ
ጥራት ያለው፣ ወቅታዊና ተደራሽ የሆነ መረጃ ለህብረተሰቡ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ለማድረስ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የሚዛን ቅርንጫፍ ጣቢያ አስታወቀ
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ