በወላይታ ሶዶ ከተማ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ
ዛሬ ከቀኑ ከ7:20 ኮድ (3)63419 ET የተሰኘ የፍሳሽ ማስወገጃ ተሽከርካሪ ባደረሰው የትራፊክ አደጋ እስካሁን የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን የሶዶ ከተማ ፖሊሲ ዋና አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገልፀዋል።
የአደጋው መንስኤ በጉዞ ላይ የነበረ ፍሳሽ ማስወገጃ መኪና ባገጠመው የቴክኒክ ችግር ሳቢያ ፍሬን አልታዘዝ ብሎት አደጋው መድረሱን ምክትል ኮማንደር ጠቁመዋል ።
በአደጋው ለህልፈት የተዳረጉት ሁለቱ በመንገድ ላይ የነበሩ የሌላ ተሸከርካሪ ረዳቶችና አንድ የሊስትሮ ባለሙያ
መሆኑን ታውቋል። ከባድ አደጋ የደረሰባቸው 3 ሰዎችም የህክምና እርዳታ እያገኙ ነው ፡፡
አደጋ አድራሹ ተሽከርካሪ መንገድ ዳር በነበሩ 6 ተሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ የንብረት ጉዳት ማድረሱን ምክትል ኮማንድሩ ተናግረዋል ፡፡
ዘጋቢ ፡ በቀለች ጌቾ

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ