የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ልዑክ ለወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ሥራና የእርስ በእርስ ግንኙነት ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ታርጫ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “በጎነት ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ልዑክ ለወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ሥራና የእርስ በእርስ ግንኙነት ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ታርጫ ከተማ ገብተዋል፡፡
ልዑኩ ታርጫ ከተማ ሲደርስ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራ እና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዐቢይ አደሞን ጨምሮ የክልልና ዳዉሮ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ብልጽግና ፓርቲ ያነገበዉን የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት በወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች የበጎ ስራና የእርስ በእርስ ግንኙነት ማጠናከር የቡድኑ ዓላማ እንደሆነም ነው የተገለጸው።
በሀገር ደረጃ ለሚገነባው የገዢ ትርክት እሳቤና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር የወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ሥራና የርስ በእርስ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑም ተገልጿል።
የክልሉ ወጣቶች ክንፍ አመራር አባላት በከተማው በሚኖራቸው ቆይታ የልማት ሥራዎች ጉብኝት፣ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላና የበጎ ስራዎች እንደሚያከናውኑ ይጠበቃል።
በመርሃ ግብሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የወጣቶች ክንፍ አመራሮች፣ የ12ቱም ዞኖችና የ3ቱ ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች የወጣቶች ክንፍ አመራሮች ተገኝቷል።
ዘጋቢ፡ መሳይ መሠለ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ