የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ልዑክ ለወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ሥራና የእርስ በእርስ ግንኙነት ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ታርጫ ከተማ ገቡ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) “በጎነት ለአብሮነት” በሚል መሪ ቃል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ልዑክ ለወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ሥራና የእርስ በእርስ ግንኙነት ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ታርጫ ከተማ ገብተዋል፡፡
ልዑኩ ታርጫ ከተማ ሲደርስ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሥራ እና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዐቢይ አደሞን ጨምሮ የክልልና ዳዉሮ ዞን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ብልጽግና ፓርቲ ያነገበዉን የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት በወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች የበጎ ስራና የእርስ በእርስ ግንኙነት ማጠናከር የቡድኑ ዓላማ እንደሆነም ነው የተገለጸው።
በሀገር ደረጃ ለሚገነባው የገዢ ትርክት እሳቤና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር የወጣቶች ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ሥራና የርስ በእርስ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑም ተገልጿል።
የክልሉ ወጣቶች ክንፍ አመራር አባላት በከተማው በሚኖራቸው ቆይታ የልማት ሥራዎች ጉብኝት፣ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላና የበጎ ስራዎች እንደሚያከናውኑ ይጠበቃል።
በመርሃ ግብሩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የወጣቶች ክንፍ አመራሮች፣ የ12ቱም ዞኖችና የ3ቱ ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች የወጣቶች ክንፍ አመራሮች ተገኝቷል።
ዘጋቢ፡ መሳይ መሠለ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ23ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛና በማታ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 347 ተማሪዎችን አስመረቀ
በ2018 በጀት ዓመት የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል – አቶ ፍቅሬ አማን
ሚዲያን ለአዎንታዊ ነገር በመጠቀም ወጣቱ ሀገርን መገንባት አለበት – የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን