የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች ለ15ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 200 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው
ተመራቂ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በቀሰሙት እውቀት ማህበረሰባቸውንና ሀገራቸውን ለማገልገል የድርሻቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።
ተማሪዎቹ ታማኝ ስራ ወዳድ ታታሪና ከስሜታዊነት ይልቅ በምክንያታዊነት የሚያምኑ በስነ-ምግባር የታነጹ እንዲሁም ድህነትን የሚጸየፉ ሊሆኑ እንደሚገባ ተመላክቷል።
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ የትምህርት ጥራት እንዲረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት በርካታ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
በመረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ የባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ጀነራል እና የዩኒቪርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ አባል ፕሮፌሰር ካሳሁን ተስፋዬ፣ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋሪስ ደሊል፣ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የተማሪ ወላጆች እየተሳተፉ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ አስቻለው አማረ – ከወልቂጤ ጣቢያችን
More Stories
የአካባቢ ብክለትን በዘላቂነት በመከላከል የተሻለች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የተገኘውን የሀይማኖት ነፃነት ማስቀጠል የሁሉም ድርሻ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የኡለማ ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ ሸክ መሀመድ ዘይን ዘይረዲን ተናገሩ
የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ፍትሃዊ አገልግሎት ለማህበረሰቡ መስጠት ላይ ትኩረት አድርገው መስራት አለባቸው – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)