የጎፋ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ አቶ ቦራና ቦሎ፤ የህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የአሰራር ስርዓትን ማጠናከር፣ የአረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለመጨመር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረው የቤተሰብ ቀን ሥራና ገቢ የተፈጠረለት የተሻለ ቤተሰብ ለመመሥረት ያለመ መሆኑን አመላክተዋል።
የዞኑ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የመንግሥት ረዳት ተጠሪ አቶ ይሁን ደምሴ፤ ሀገርን የሚገነባ ትውልድ ለመፍጠር የስነ-ምግባር ብልሹነትን ለማረም በኢኮኖሚና በአሰተሳሰብ ጠንካራ ቤተሰብ የመፈጠር ሥራ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የመምሪያው ማህበራዊ ደንነት ዋና ሥራ ሂደት አሰተባባሪ አቶ ዘርሁን ጊያ፤ በከተማና በገጠር የሥራ ልምምድን በማሻሻል በጠንካራ የሥራ ባህል የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ሰነድ አቀርበዉ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የጎፋ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ሀብታምነሽ ግራዝማች፤ ለአካባቢው ሰላምና ደህንነት መጠበቅ፣ የቤተሰብ ሥራና ገቢ መጨመር ሀገር ለመገባንት ያለው ሚና የጎላ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የውይይቱ ተሳታፊዎች የሥራ ባህልን በማሳደግ በተለይ በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ ለወጣቱ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችል ሰፊ ዕድል መኖሩን አንስተዋል።
ዘጋቢ፡ ሰንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ