በመደረኩ የተገኙት የዞኑ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ዘውዱ ሳሙኤል እንዳሉት፤ ሴቶች ለሀገር ግንባታ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና በፖለቲካ እያበረከቱ ያለው አስተዋዕጾ የጎላ መሆኑን በመጠቆም ያለሴቶች ተሳትፎ ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ አይቻልም።
በዞኑ በርካታ ሴቶች በአካባቢ የሚገኙ ፀጋዎችን በመጠቀም ኑሮአቸውን እንደለወጡም ተናግረዋል።
የወላይታ ዞን የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመንግስት ረዳት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል በበኩላቸው፤ እንደ ወላይታ ዞን ሴቶች በሁሉም ዘርፍ በመሳተፋቸው አበረታች ለውጦች እንዲመዘገቡ ማድረጉን ተናግረዋል።
ሴቶችን በውሳኔ ሰጪነት ለማብቃት ፓርቲዉ ከምንጊዜዉም በላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በርካታ ሴቶች በአረንጓዴ አሻራ፣ በህግ ማስከበር፣ በመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ፣ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ፣ ለትምህርት ቤቶች የመማሪያ መጽሀፍት ግዢ ዙርያ የሴቶች ተሳትፎ የጎላ መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
በመድረኩ የተገኙ ሴቶች በሰጡት ሀሳብ በአካባቢያቸው በመጣው ለውጥ በርካታ ሴቶች ወደ ዉሳኔ ሰጪነት በማደጋቸው የሚታይ ለውጥ በመምጣት ላይ ይገኛል ብለዋል።
እንደ ዞን በርካታ ሴቶች ችሎታ እያላቸው እድል አጥተው የተቀመጡ ሴቶችን የፓርቲው ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አሁንም ማብቃት እንዳለበት ተናግረዉ፤ በትምህርት ዕድሎች ላይ ትኩረት ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡
ዘጋቢ፡ በቀለች ጌቾ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ