በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የም ዞን ከዞኑ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ውይይት እየተደረገ ነው
ሀዋሳ፡ ግንቦት 16/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የም ዞን “ትውልድ በመምህር ይቀረፃል፤ ሀገር በትምህርት ይበለፅጋል” በሚል መሪ ቃል ከዞኑ ከተውጣጡ መምህራን ጋር በሣጃ ከተማ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡
የውይይት መድረኩ ባለፉት ጊዜያት በዞኑ በሁሉም አስተዳደር መዋቅሮች ሲካሄድ የቆየ ሲሆን በዛሬው ዕለትም የሚካሄደው ዞናዊ የማጠቃለያ ውይይት መሆኑ ተገልጿል።
የውይይቱ ዓላማም በትምህርት ልማት ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችና እየተስተዋሉ ያሉ ጉድለቶችን እንዲሁም ቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ መግባባት ለመፍጠር ነው።
በውይይቱ ላይ የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሽመልስ እጅጉ፣ የዞኑ የመንግስት ተጠሪ አቶ አብርሃም ዝናብን ጨምሮ የዞንና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም መምህራን እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ከውይይቱ አስቀድሞ የዞኑ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እና ተሣታፊዎች በሣጃ ከተማ እየተሠሩ ያሉ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ማሙዬ ፊጣ – ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ