ለኢትዮጵያ ቀጣይ ጉዞ የሚዲያ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በዲላ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የጌዴኦ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ዜና ማሞ፤ ሚዲያዎች ከተቋቋሙለት ዓላማ አንጻር ተአማኒነት ያላቸውን መረጃዎች ለህብረተሰቡ ከማድረስ ባሻገር አካባቢን የማስተዋወቅ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረቱ ተፈሪ፤ በሀገር ግንባታ ረገድ ሚዲያዎች ያላቸው ሚና ቀላል የማይባል እንደሆነ ገልፀው ሁሉም ሃላፊነታቸውን በሚገባ እንዲወጡ አሳስበዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ: ለምለም ኦርሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

                
                                        
                                        
                                        
                                        
More Stories
በኮሪደር ልማት፣ የመንገድ ግንባታ እና ተያያዥ ስራዎች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ የጠቅላላ ተቋራጮች እና የአገልግሎት ተቋማት ትጋትና ቁርጠኝነት የሚበረታታ መሆኑ ተገለጸ
በሴቶች ላይ የሚደርሱ ማህበራዊ ጫናዎችን ለመከላከል የኢኮኖሚ ባለቤት እንዲሆኑ ለማስቻል ሁሉም ባለድርሻ አካላላት ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ ተገለፀ
ትምህርት ቤቶች የዉስጥ ገቢያቸዉን በማሳደግ የግብዓት ችግሮችን በመቅረፍ ምቹ የመማር ማስተማር ከባቢን መፍጠር እንዳለባቸዉ ተገለፀ