ለኢትዮጵያ ቀጣይ ጉዞ የሚዲያ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በዲላ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የጌዴኦ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ዜና ማሞ፤ ሚዲያዎች ከተቋቋሙለት ዓላማ አንጻር ተአማኒነት ያላቸውን መረጃዎች ለህብረተሰቡ ከማድረስ ባሻገር አካባቢን የማስተዋወቅ ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው ብለዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረቱ ተፈሪ፤ በሀገር ግንባታ ረገድ ሚዲያዎች ያላቸው ሚና ቀላል የማይባል እንደሆነ ገልፀው ሁሉም ሃላፊነታቸውን በሚገባ እንዲወጡ አሳስበዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ: ለምለም ኦርሳ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት፣ ቁጥጥርና የደረጃ ምዘና የአሰራር ስርዓት ለውጥ እየታየበት መምጣቱ ተገለጸ
በወሊድ ምክንያት የሚሞቱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስ የተጀመሩ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
የፃማኮ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ የ”ባርባይሳ” በዓል የህብረ ብሄራዊ አንድነት መገለጫ፣ የሰላምና የመተሳሰብ ምልክትነቱን በማግዘፍ ለዓለም አደባባይ ማብቃት ይገባል ሲሉ የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ገለጹ