በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዱራሜ ክላስተር የግብርና ሴክተር ባለሙያዎች “የመሐሉ ዘመን” በሚል ርዕስ ወቅታዊና ሀገራዊ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄዱ
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር የስልጠናና የውይይት ሰነዱን ለሴክተሩ ባለሙያዎች እንዳብራሩት፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ የረጂም ጊዜ የፖለቲካ ታሪክ ያላትና በስኬትም በውድቀትም ያለፈችና የፀናች ሀገር ናት።
አቶ ኡስማን እንዳሉት፤ እየገጠሙን ያሉ ፈተናዎችን ወደ ዕድል እንዲሁም ዕድሉን ወደ ውጤት መቀየር ያስፈልጋል።
ባለፉት ዓመታት በተመዘገቡት ድሎች ሳንረካ በቀጣይም ሌሎች ስኬቶችን ማስመዝገብ ይጠበቅብናልም ብለዋል።
የግብርና ሴክተር የተለየ ተልዕኮ የሰነቀ መሆኑን ተገንዝበን ለሀገራዊ ስኬት በተሰማራንበት በሁሉም መስኮች መትጋት ግድ ይላል በማለት ገልፀዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዱራሜ ክላስተር የግብርና ሴክተር ባለሙያዎች የመሐሉ ዘመን በሚል ርዕስ በተካሄደው ወቅታዊና ሀገራዊ ውይይት “የመሐሉ ዘመን” ምንነት፣ ፍይዳና ፈተናዎችን በውል ለመረዳት የሚያስችል እንደሆነም ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ታደሰ

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ