የስልጤ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 29 መደበኛ ጉባዬውን ማካሄድ ጀመረ
የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉበኤ ወ/ሮ መህዲያ ቡሴር በጉባኤው መክፈቻ እንደገለጹት፥ በ29ኛ መደበኛ ጉባኤ የ9 ወር ሪፖርት ማቅረብ፣ የ28ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃላ-ጉባኤ መርምሮ በማጽደቅ ነው የዕለቱ ጉባኤ የጀመረው፡፡
በአሁኑ ሰዓት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ የዘጠኝ ወር ሪፖርት እየቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት መሰረት ከምክር ቤት አባላት አስተያየት እና ጥያቄ ቀርቦ ውይይት እና ማብራሪያ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሙጂብ ጁሃር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከል በሚደረገው አገራዊ ጥረት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅምና መብት በማስጠበቅ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ