የስልጤ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 29 መደበኛ ጉባዬውን ማካሄድ ጀመረ
የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉበኤ ወ/ሮ መህዲያ ቡሴር በጉባኤው መክፈቻ እንደገለጹት፥ በ29ኛ መደበኛ ጉባኤ የ9 ወር ሪፖርት ማቅረብ፣ የ28ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃላ-ጉባኤ መርምሮ በማጽደቅ ነው የዕለቱ ጉባኤ የጀመረው፡፡
በአሁኑ ሰዓት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ የዘጠኝ ወር ሪፖርት እየቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት መሰረት ከምክር ቤት አባላት አስተያየት እና ጥያቄ ቀርቦ ውይይት እና ማብራሪያ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: ሙጂብ ጁሃር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ