በክልሉ የሻይ ተክል ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ገለጹ
በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሸ ዋጌሾ(ዶ/ር) የተመራ የከፍተኛ አመራሮች ቡድን በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ ቦጊንዳ የሻይ ችግኝ ጣቢያን ጎብኝቷል፡፡
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው የሻይ ተክል ስራ በክልሉ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸው፤ በወረዳው ቦጊንዳ ቀበሌ እየተዘጋጀ ያለው የዚሁ አንዱ ማሣያ ነው ብለዋል፡፡
በወረዳው የቦጊንዳ ቀበሌ የሰብል ባለሙያ አቶ ማሙሽ ገብሬ፤ የሻይ ችግኝ ተከላ ከዚህ ቀደም በነበረው ጊዜ ያልተለመደ መሆኑን ገልጸዋል።
የቦጊንዳ የሻይ ችግኝ ጣቢያ ለ2018 ዓመተ ምህረት በወረዳው የተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች የሚሰራጭ የሻይ ችግኝ የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
500 ሺህ የሻይ ችግኝ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስከአሁን ባለው 180 ሺህ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡
በጉብኝቱ የክልሉ ርዕስ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)፣ በክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ በላይ ተሰማ፣ በምክትል ርዕሰ መሰተዳደር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴና ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ ሀላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ብዙአየሁ ጫካ – ከቦንጋ ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ