በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን ባህል በማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራን ማጎልበት ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አሳሰቡ
በጋርዱላ ዞን በዲራሼ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየአካባቢው በመተግበር የተራቆቱ ተራሮችን ዳግም እንዲያገግሙ እየተደረገ ይገኛል።
የዚህ ተግባር አንድ አካል የሆነው በጋርዱላ ዞን በዲራሼ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ተካሂዷል።
በተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳኤ እንደተናገሩት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ልዩነት ለማጥበብ እድል ይሰጣል።
በሀገሪቱ ለባለፉት በርካታ አመታት እነዚህ መርሃ ግብሮች መከናወናቸውን ተከትሎ አለም ያረጋገጠውና የሚጨበጥ ለውጥ ተመዝግቧልም ብለዋል።
በጋርዱላ ዞን የዲራሼ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኪስሞ ኪታንቦ በበኩላቸው፤ በወረዳው በዚህ መርሃ ግብር 47 ሄክታር መሬትን በተለያዩ ሀገር በቀል ችግኞች ለመሸፈን መቻሉንም ተናግረዋል።
የችግኝ ተከላው በወረዳው በከፍተኛ ሁኔታ የሚከሰተውን የመሬት ናዳና የጎርፍ አደጋን ለመከላከል አይነተኛ አጋዥ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ ይህም ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት ከዚህ ቀደም ይደርስባቸው የነበረው ጎርፍና ናዳን በየጊዜው በሚካሄደው የችግኝ ተከላ ማስታገስ መቻሉን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል