በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን ባህል በማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራን ማጎልበት ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አሳሰቡ
በጋርዱላ ዞን በዲራሼ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየአካባቢው በመተግበር የተራቆቱ ተራሮችን ዳግም እንዲያገግሙ እየተደረገ ይገኛል።
የዚህ ተግባር አንድ አካል የሆነው በጋርዱላ ዞን በዲራሼ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ተካሂዷል።
በተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳኤ እንደተናገሩት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ልዩነት ለማጥበብ እድል ይሰጣል።
በሀገሪቱ ለባለፉት በርካታ አመታት እነዚህ መርሃ ግብሮች መከናወናቸውን ተከትሎ አለም ያረጋገጠውና የሚጨበጥ ለውጥ ተመዝግቧልም ብለዋል።
በጋርዱላ ዞን የዲራሼ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኪስሞ ኪታንቦ በበኩላቸው፤ በወረዳው በዚህ መርሃ ግብር 47 ሄክታር መሬትን በተለያዩ ሀገር በቀል ችግኞች ለመሸፈን መቻሉንም ተናግረዋል።
የችግኝ ተከላው በወረዳው በከፍተኛ ሁኔታ የሚከሰተውን የመሬት ናዳና የጎርፍ አደጋን ለመከላከል አይነተኛ አጋዥ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ ይህም ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት ከዚህ ቀደም ይደርስባቸው የነበረው ጎርፍና ናዳን በየጊዜው በሚካሄደው የችግኝ ተከላ ማስታገስ መቻሉን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ