በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄን ባህል በማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራን ማጎልበት ይገባል ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አሳሰቡ
በጋርዱላ ዞን በዲራሼ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በየአካባቢው በመተግበር የተራቆቱ ተራሮችን ዳግም እንዲያገግሙ እየተደረገ ይገኛል።
የዚህ ተግባር አንድ አካል የሆነው በጋርዱላ ዞን በዲራሼ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ተካሂዷል።
በተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳኤ እንደተናገሩት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ልዩነት ለማጥበብ እድል ይሰጣል።
በሀገሪቱ ለባለፉት በርካታ አመታት እነዚህ መርሃ ግብሮች መከናወናቸውን ተከትሎ አለም ያረጋገጠውና የሚጨበጥ ለውጥ ተመዝግቧልም ብለዋል።
በጋርዱላ ዞን የዲራሼ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኪስሞ ኪታንቦ በበኩላቸው፤ በወረዳው በዚህ መርሃ ግብር 47 ሄክታር መሬትን በተለያዩ ሀገር በቀል ችግኞች ለመሸፈን መቻሉንም ተናግረዋል።
የችግኝ ተከላው በወረዳው በከፍተኛ ሁኔታ የሚከሰተውን የመሬት ናዳና የጎርፍ አደጋን ለመከላከል አይነተኛ አጋዥ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ ይህም ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በችግኝ ተከላው ላይ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላት ከዚህ ቀደም ይደርስባቸው የነበረው ጎርፍና ናዳን በየጊዜው በሚካሄደው የችግኝ ተከላ ማስታገስ መቻሉን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: በኃይሉ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ