ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
“ዓላማ ተኮር ተግባቦት ለኢትዮጰያ መንሠራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ተገልጿል።
የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ዜና ማሞ በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፋ ሲሆን፤ ተአማኒነት ያላቸውን መረጃዎች ለማህበረሰቡ ተደራሽ በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ዕውን ማድረግ አለብን ብለዋል።
የማህበረበሰቡን ሁሉ አቀፍ የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራው ተአማኒነት ያለው መረጃ ተደራሽ ማድረግ ስላለበት የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመሙላት የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አስገንዝበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሀላፊና የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ አዜብ ዘዉዱ፤ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት በማጠናከር ተአማኒነት ያለውን መረጃ በማድረስ በሀገራችን የተጀመሩ ለውጦችን ማስገንዘብ እንዲቻል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል።
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ከመንግስት ጋር በመሆን የመንግስት የትኩረት አቅጣጫዎችን እንዲሁም ከነጠላ ትርክት በመውጣት የገዥ ትርክት ግንባታ ሚና ስራዎች ላይ ሚዲያ በበላይነት ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተአማኒነት ያለውን መረጃ ተደራሽ በማድረግ የተግባቦት ሚናውን ማጠናከር ይጠበቅበታል ነው ያሉት።
በመድረኩ የክልልና የዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሀላፊዎች የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ስራዎቻችን በመንግስትና በማህረሰቡ ዘንድ ተግባቦትን ለማጠናከር በምን መልኩ መተግበር እንዳለባቸውና ያሉ ማነቆዎችን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነዶችን አቅርበዋል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮችና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ታድመዋል።
ዘጋቢ፡ ጽጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል