ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
“ዓላማ ተኮር ተግባቦት ለኢትዮጰያ መንሠራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ተገልጿል።
የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ዜና ማሞ በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፋ ሲሆን፤ ተአማኒነት ያላቸውን መረጃዎች ለማህበረሰቡ ተደራሽ በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ዕውን ማድረግ አለብን ብለዋል።
የማህበረበሰቡን ሁሉ አቀፍ የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራው ተአማኒነት ያለው መረጃ ተደራሽ ማድረግ ስላለበት የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመሙላት የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አስገንዝበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሀላፊና የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ አዜብ ዘዉዱ፤ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት በማጠናከር ተአማኒነት ያለውን መረጃ በማድረስ በሀገራችን የተጀመሩ ለውጦችን ማስገንዘብ እንዲቻል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል።
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ከመንግስት ጋር በመሆን የመንግስት የትኩረት አቅጣጫዎችን እንዲሁም ከነጠላ ትርክት በመውጣት የገዥ ትርክት ግንባታ ሚና ስራዎች ላይ ሚዲያ በበላይነት ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተአማኒነት ያለውን መረጃ ተደራሽ በማድረግ የተግባቦት ሚናውን ማጠናከር ይጠበቅበታል ነው ያሉት።
በመድረኩ የክልልና የዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሀላፊዎች የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ስራዎቻችን በመንግስትና በማህረሰቡ ዘንድ ተግባቦትን ለማጠናከር በምን መልኩ መተግበር እንዳለባቸውና ያሉ ማነቆዎችን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነዶችን አቅርበዋል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮችና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ታድመዋል።
ዘጋቢ፡ ጽጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ