ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
“ዓላማ ተኮር ተግባቦት ለኢትዮጰያ መንሠራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ተገልጿል።
የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ሀላፊ ወ/ሮ ዜና ማሞ በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፋ ሲሆን፤ ተአማኒነት ያላቸውን መረጃዎች ለማህበረሰቡ ተደራሽ በማድረግ የብልጽግና ጉዞን ዕውን ማድረግ አለብን ብለዋል።
የማህበረበሰቡን ሁሉ አቀፍ የልማት ተሳታፊና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራው ተአማኒነት ያለው መረጃ ተደራሽ ማድረግ ስላለበት የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመሙላት የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አስገንዝበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሀላፊና የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ አዜብ ዘዉዱ፤ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት በማጠናከር ተአማኒነት ያለውን መረጃ በማድረስ በሀገራችን የተጀመሩ ለውጦችን ማስገንዘብ እንዲቻል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል።
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ከመንግስት ጋር በመሆን የመንግስት የትኩረት አቅጣጫዎችን እንዲሁም ከነጠላ ትርክት በመውጣት የገዥ ትርክት ግንባታ ሚና ስራዎች ላይ ሚዲያ በበላይነት ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተአማኒነት ያለውን መረጃ ተደራሽ በማድረግ የተግባቦት ሚናውን ማጠናከር ይጠበቅበታል ነው ያሉት።
በመድረኩ የክልልና የዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሀላፊዎች የሚዲያና የኮሙኒኬሽን ስራዎቻችን በመንግስትና በማህረሰቡ ዘንድ ተግባቦትን ለማጠናከር በምን መልኩ መተግበር እንዳለባቸውና ያሉ ማነቆዎችን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነዶችን አቅርበዋል።
በመድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮችና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ታድመዋል።
ዘጋቢ፡ ጽጌ ደምሴ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ