የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ክልላዊ መድረክ እየተካሄደ ነዉ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ክልላዊ መድረክ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በወላይታ ሶዶ እየተካሄደ ይገኛል።
”የመሃሉ ዘመንን መረዳት” በሚል ሃሳብ እየተካሄደ ባለው በዚሁ መድረክ፤ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መድረኩ የተዘጋጀው ባለፉት ሰባት የለውጡ አመታት በክልሉ ብሎም በሀገሪቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን በቀጣይም በዘላቂነት ለማስቀጠል ነው።
መድረኩ በተለይ የህዝብን አንድነት በማጠናከርና ያሉትን ፈተናዎች ወደ ድል በመቀየር የሚፈለገውን ብልጽግና ለማረጋገጥ እንደሆነም ነዉ ርዕሰ መስተዳድሩ የገለፁት።
የተመዘገቡት ስኬቶችን የበለጠ ዉጤታማ ለማድረግ አመራሩ ይበልጥ እንዲዘጋጁ የሚያስችል መድረክ መሆኑን አቶ ጥላሁን ጥላሁን ከበደ አስረድተዋል።
በመድረኩ “የመሐሉ ዘመን” በሚል ሃሳብ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ከክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ