ቀልጣፋ የመንገድና ትራንስፖርት አገልግሎት በለለበት ልማትን ማሳለጥ የሚቻል ባለመሆኑ፣ የገጠር መንገድ ትራንስፖርት እና መንገድ አገልግሎትን ለማጠናከር በየደረጃችን ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል-አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በአዲሱ በሰው ሀብት አሰራር መመሪያዎች፣ በሙስና ወንጀሎች እና በስራ ስነምግባር ላይ ለዞኖች ፣ ከተማ አስተዳደሮች ሰው ሀብት አስተዳደር ልማት አስተባባሪዎች እና ለተቋሙ ሠራተኖች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በይርጋጨፌ ከተማ እያካሄደ ነው።
በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይለማርያም ተስፋዬ እንደተናገሩት፣ ቀልጣፋ የመንገድና ትራንስፖርት አገልግሎት በሌለበት ልማትን ማሳለጥ የሚቻል ባለመሆኑ፣ የገጠር መንገድ ትራንስፖርት እና መንገድ አገልግሎትን ለማጠናከር በየደረጃው ርብርብ ማድረግ ያስፈልጋል።
የሕዝቡን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መሠረት በማድረግ፣ በፌደራል እና በክልሉ አቅም በየደረጃው የሚሠሩ የመንገድ ልማቶችን መለየት እና ኢኮኖሚን መደገፍ በሚችል መልኩ መገንባት እንደሚያስፈልግም አቶ ኃይለማሪያም ተናግረዋል።
ሕብረተሰቡን በመንገድ ልማት ጉዳይ ላይ ባለቤት እንዲህኑ በማድረጉ ረገድ ክፍተት ያለ በመሆኑ በቀጣይ ትኩረት ሊሆን እንደሚገባም አመላክተዋል።
የትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ደሕንነቱ የተጠበቀ ካልሆነ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳቱ ከፍተኛ በመሆኑ ጉዳት ለመቀነስ በጥናት በትኩረት እንዲሰራም አሳስበዋል።
ዘርፉ ሰፊ ሀብት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ ምስጉን ሠራተኝችን ማፍራት ላይ ቢሮው ትኩረት አድርጎ እየሠራ ነው ያሉት አቶ ኃይለማሪያም፣ የግንዛቤ ማስጨበጫው ይህንን የሚደግፍ መሆኑን ተናግረዋል።
ዘጋቢ : እስራኤል ቅጣው – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት በሸማቾች ማህበር የሚቀርቡ ምርቶች ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ሸማቾች ተናገሩ
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2017 ዓ.ም የተገልጋይ ውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነው
የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የእንግሊዝኛ ቋንቋ ተግባቦትን ማሳደግ እንደሚገባ ተገለጸ