በሆስፒታሉ የአገልግሎት መስጫ አካባቢዎች የመስክ ምልከታም ተደርጓል።
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት ኢሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው በመግቢያ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት፤ ሆስፒታሉ በሰብ ስፔሻሊቲና ስፔሻሊቲ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ ከዚህ ቀደም ከህብረተሰቡ የሚነሱ የተለያዩ የአገልግሎት ችግሮች ይስተዋሉ እንደነበር አንስተው፤ የሆስፒታሉ የማኔጅመንት አባላት ባደረጉት የጋራ ርብርብ ዘርፈ ብዙ ለውጦች እየታዩ መጥተዋል ብለዋል።
ውይይቱ ያሉብንን ጉድለቶች በመሸፈን ለተገልጋዮች ተገቢውን የህክምናና አስፈላጊ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑን አመላክተዋል።
በውይይት መድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶና የዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንትና የሴኔት አባላትን ጨምሮ የዞንና የክልል ባለድርሻ አካላትና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
በውይይቱም ህብረተሰቡን የሚያረካ ተገቢውን የህብረተሰብ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንደሚያዝ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ