በሆስፒታሉ የአገልግሎት መስጫ አካባቢዎች የመስክ ምልከታም ተደርጓል።
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት ኢሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው በመግቢያ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት፤ ሆስፒታሉ በሰብ ስፔሻሊቲና ስፔሻሊቲ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።
ይሁን እንጂ አልፎ አልፎ ከዚህ ቀደም ከህብረተሰቡ የሚነሱ የተለያዩ የአገልግሎት ችግሮች ይስተዋሉ እንደነበር አንስተው፤ የሆስፒታሉ የማኔጅመንት አባላት ባደረጉት የጋራ ርብርብ ዘርፈ ብዙ ለውጦች እየታዩ መጥተዋል ብለዋል።
ውይይቱ ያሉብንን ጉድለቶች በመሸፈን ለተገልጋዮች ተገቢውን የህክምናና አስፈላጊ አገልግሎቶችን ተደራሽ በማድረግ የህብረተሰቡን እርካታ ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅኦ ያለው መሆኑን አመላክተዋል።
በውይይት መድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቴዎስ አኒዮ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶና የዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንትና የሴኔት አባላትን ጨምሮ የዞንና የክልል ባለድርሻ አካላትና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛል።
በውይይቱም ህብረተሰቡን የሚያረካ ተገቢውን የህብረተሰብ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንደሚያዝ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ