ለትንሣኤ በዓል አንድ ሳምንት ሲቀር የሚከበረው የሆሳዕና በዓል “ሆሣዕናን በሆሳዕና” በሚል መንፈሳዊ መርህ በሆሳዕና መምበረ ጵጵስና ደ/ገነት ቅድስት ማርያም ቤ/ያን እየተከበረ ነው
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 05/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን በየዓመቱ ለትንሣኤ በዓል አንድ ሳምንት ሲቀር የሚከበረው የሆሳዕና በዓል “ሆሣዕናን በሆሳዕና” ከተማ በሚል መንፈሳዊ መርህ በሆሳዕና መምበረ ጵጵስና ደ/ገነት ቅድስት ማርያም ቤ/ያን እየተከበረ ይገኛል።
በዓሉ ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ውርንጭላ ሆኖ ከገሊላ ናዝሬት ወደ ኢየሩሳሌም የገባበትን አብነት በማድረግ የሚከበር ስለመሆኑ አባቶችና መምህራነ ወንጌል በአስተምህሮታቸው ገልፀዋል።
በእለቱም የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣት የተመለከቱ የዘምባባ ዝንጣፊ እንዳነጠፉ ምዕመናኑ ዘምባባ እያነጠፉና በግባራቸውም በማሰር ስርዓቱን እንደሚያከብሩት ተናግረዋል።
በዓሉ ሲከበር ምዕመናኑ በሠላም፣ በፍቅር እንዲሁም እርስ በርስ በመተሳሰብና ሁሉም ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ሠላም ዘብ በመቆም ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዓሉ በየዓመቱ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት የሚከበር ሲሆን በዘንድሮ ዓመትም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ መምህራነ ወንጌልና ዘማሪያን እንዲሁም፥ ምዕመናን በተገኙበት በሆሳዕና መምበረ ጵጵስና ደ/ገነት ቅድስት ማርያም ቤ/ያን በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት እየተከበረ ነው።
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ