መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ፣ የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሀመድ ኑሪዬ እንደገለፁት፤ የመድረኩ ዋና ዓላማ በገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና ፕሮግራም አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ነዉ።
ፕሮግራሙ በሀገር ደረጃ ገጠርን መሰረት አድርጐ እየተተገበረ የሚገኝ መሆኑት የገለጹት የቢሮው ሃላፊ፤ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም በ8 ወረዳዎች ፕሮግራሙ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በፕሮግራሙ የመንገድ ግንባታና ጥገና እንዲሁም የተንጠልጣይ ድልድይ ስራዎች የተከተቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ በ8ቱም ወረዳዎች 111 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የመንገድ ግንባታ፣ 132 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጥገና እንዲሁም 5 የተንጠልጣይ ድልድዮች እና ዘጠኝ ልዩ ልዩ ስትራክቸሮች በፕሮግራሙ የሚከናወኑ መሆኑን ዶ/ር መሀመድ ጠቁመዋል።
ፕሮግራሙ ለክልሉ ያለው ፋይዳ ከፍተኛ ነው ያሉት የቢሮው ሃላፊ፤ እስካሁን ፕሮግራሙ በተሳካ ሁኔታ እንዲሄድ እያደረጉ የሚገኙ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላትን አመሰግነዋል።
በቀጣይ ጊዜም ፕሮግራሙን በልዩ ሁኔታ የመደገፍ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።
በመድረኩ የገጠር ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና (RCFSP) ፕሮግራም የ9 ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን በተመረጡ አካባቢዎች ላይ የመስክ ምልከታ እንደሚደረግም ተገልጿል።
ዘጋቢ: ተሻለ ከበደ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ