በጎፋ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት የፍትህ ተቋማት ትራንስፎርሜሽን ዞናዊ የንቅናቀ መድረክ በሳውላ ከተማ ተካሂዷል፡፡
የጎፋ ዞን የሕዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሀብታምነሽ ግራአዝማች የንቅናቄ መድረኩን ሲከፍቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የፍትህ ተቋማትና ፍርድ ቤቶች ውጤታማና ቀልጣፋ አገልግሎት ለህብረተሰቡ በመሰጠት የሚነሱ ቅሬታዎችን በአግባቡ መፍታት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡
የጎፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኘሬዚዳንት አቶ ፀጋዬ ፅጌ፤ በየደረጃው የሚገኙ ፍርድ ቤቶች የፍትህ አገልግሎት ለመሰጠት የሰለጠነ የሰው ሀይል በማደራጀትና በቴክኖሎጂ የታገዙ ሰራዎች ለመሰራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡
የፍትህ ተቋማት ለህብረተሰቡ ጥብቅና በመቆም ማገልገል እንዳለባቸው አንሰተው፤ ከስነ- ምግባር አኳያ የሚነሱ ቅሬታዎች በቀጣይ በትኩረት የሚፈታ መሆኑን የዞኑ ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ ብላቴ ተናግረዋል፡፡
የወይይቱ ተሳታፊዎች በፍትህ ተቋማት የሚስተዋሉ የፍትህ አሰጣጥ ችግሮችን በመቅረፍ በበጀት እጥረት የሚነሱ ጥያቄዎች እና በሴቶችና ህጻናት ጉዳይ የሚሰተዋሉ የፍትህ አሰጣጥ ችግሮች እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡
የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የከተማ መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ኤርምያሰ ሁሰኔ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ስንታየሁ ሙላቱ – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል