ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑ ተገለጸ
ከ12 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ማሰራጨቱን የኮሬ ዞን ግብርና መምሪያ አስታውቋል።
የኮሬ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አስታረቀኝ አንደባ፤ ምርታማነትን ከመጨመር ረገድ የአፈር ማዳበሪያ ወሳኝነት እንዳለውና ዘንድሮ ለበልግ እርሻ የሚውል ከ12 ሺህ ኩንታል በላይ ለአርሶአደሮች በማቅረብ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
የሰብል ልማት ጥበቃ ቡድን መሪ አቶ አሸናፊ አሳምነው በበኩላቸው፤ በዞን ደረጃ የቀረበውን የአፈር ማዳበሪያ ለወረዳዎች ማድረሳቸውንና አሁን ላይ ወረዳዎች ለአርሶ አደሮች በማሰራጨት ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል።
ከክልል ለዞን የተላከው 7 ሺህ 2 መቶ ኩንታል ዳፕ እና 4 ሺህ 8 መቶ ኩንታል ዩሪያ በድምሩ 12 ሺህ ኩንታል መቅረቡን የገለጹት አስተባባሪው አሁን ላይ በሁሉም አካባቢዎች ስርጭት እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል።
በዞን ደረጃ እስከአሁን ከተሰራጨው ማዳበሪያ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ መሰብሰቡንና ከ8 ሚሊዮን በላይ ገንዘብ ባንክ ገቢ መደረጉን የቡድን መሪው አብራርተዋል።
በማዳበሪያ አጠቃቀም ዙሪያ የአርሶ አደሮቹ ግንዛቤ እየጨመረ ከመምጣቱ የተነሳ አቅርቦቱም በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱን የተናገሩት አቶ አሸናፊ፤ ለዚህም የባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ገልጸዋል።
ከአቅርቦት ውስንነት ጋር ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት ከክልሉ ጋር በተያዘው አቅጣጫ መጋዘን ያለው ተሰራጭቶ ሲጠናቀቅ ተጨማሪ ለማስገባት ከስምምነት መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
አርሶ አደር ጉይባ ጉንአ እና ትሩፋት ጾካደ በጎርካ ወረዳ የሱሉኮና ሻፉሌ ቀበሌ ነዋሪዎች ሲሆኑ ውስንነቶች ቢኖሩም የአፈር ማዳበሪያው በጊዜ እንደደረሳቸው ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ ተሾመ ፀጋዬ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
ከበልግ እርሻ ሰብሎች 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ማቀዱን የቡርጂ ዞን ገለጸ
ወጣቱ በሥራ ዕድል ፈጠራ የነገ ህይወቱ ተቀይሮ ለሀገር እንዲተርፍ ክህሎቱን የማሳደግ ሥራ እየተሠራ እንደሆነ ተገለጸ
የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የትምህርት ግበዓት መሟላት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ