አምራች ኢንዱስትሪውን በማጠናከር ተኪ ምርቶን ለመጨመር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ገለጸ

አምራች ኢንዱስትሪውን በማጠናከር ተኪ ምርቶን ለመጨመር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ገለጸ

ቢሮው “ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት” ንቅናቄ በአርባ ምንጭ ጀምሯል።

ከ75 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከሸማቹ ጋር ያገናኘው ባዛርና ኤግዚቢሽን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በይፋ ተከፍቷል።

በመድረኩ በኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚታዩ ዕድሎች እና ተግዳሮቶች ዙሪያ የተዘጋጁ ጥናቶች ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ዘጋቢ፡ ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን