ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለሀገር አካል የሆነውን ሃላላ ኬላ ሪዞርት መርቀው ከፍተዋል፡፡
ሪዞርቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተጨማሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የክልል ርዕሳነ-መስተዳድሮችና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል፡፡
ሪዞርቱ የገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክት አካል ሲሆን÷ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በጥራት ተገንብቶ ተጠናቋል፡፡
የፕሮጀክቱ ግንባታም የአካባቢው ማኅበረሰብ ነባር የኪነ-ህንፃ ጥበብን ከዘመናዊ የግንባታ ቴክኖሎጂ ጋር በማናበብ ማራኪ በሆነ አግባብ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ነው የተባለው፡፡
ሪዞርቱ በተገነባበት ሥፍራ የሚገኘው የጊቤ ሦስት ኃይል ማመንጫ ሰው ሰራሽ ኃይቅም የሪዞርቱ ተጨማሪ ውበት መሆኑን ተጠቅሷል፡፡
በውስጡም ፕሬዚዳንታዊ የእንግዳ ማረፊያዎች፣ ዘመናዊ መኝታ ክፍሎችና ሌሎች የመዝናኛ ሥፍራዎችን የያዘ ነው፡፡
የሪዞርቱ መገንባትም ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ነው የተጠቆመው፡፡

More Stories
20ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያዊያን የምክክር ቀን መካሄድ ጀመረ
ወጣቶች በተለያዩ የስራ ዘርፎች በማህበር ተደራጅተው በመስራት ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ ገለፀ
ኮሌጁ በመደበኛና የማታ መርሃ-ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመረቀ