ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለሀገር አካል የሆነውን ሃላላ ኬላ ሪዞርት መርቀው ከፍተዋል፡፡
ሪዞርቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተጨማሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የክልል ርዕሳነ-መስተዳድሮችና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል፡፡
ሪዞርቱ የገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክት አካል ሲሆን÷ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በጥራት ተገንብቶ ተጠናቋል፡፡
የፕሮጀክቱ ግንባታም የአካባቢው ማኅበረሰብ ነባር የኪነ-ህንፃ ጥበብን ከዘመናዊ የግንባታ ቴክኖሎጂ ጋር በማናበብ ማራኪ በሆነ አግባብ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ነው የተባለው፡፡
ሪዞርቱ በተገነባበት ሥፍራ የሚገኘው የጊቤ ሦስት ኃይል ማመንጫ ሰው ሰራሽ ኃይቅም የሪዞርቱ ተጨማሪ ውበት መሆኑን ተጠቅሷል፡፡
በውስጡም ፕሬዚዳንታዊ የእንግዳ ማረፊያዎች፣ ዘመናዊ መኝታ ክፍሎችና ሌሎች የመዝናኛ ሥፍራዎችን የያዘ ነው፡፡
የሪዞርቱ መገንባትም ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ነው የተጠቆመው፡፡
More Stories
በመጀመሪያ 3 ወራት የቅድመ ወሊድ አገልግሎት በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ተጠናክሮ ሊሰራበት እንደሚገባ የኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ
ምስራቅ አፍሪካን ያመሰው ክስተት
የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ከማጠናከር ባለፈ ጤናማ ንቁና የተሻለ ስብዕና ያለው ትውልድ ለመፍጠር የቴኳንዶ ስፖርት ትልቅ ሚና እንዳለው ተመላከተ