ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለሀገር አካል የሆነውን ሃላላ ኬላ ሪዞርት መርቀው ከፍተዋል፡፡
ሪዞርቱ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተጨማሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የክልል ርዕሳነ-መስተዳድሮችና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል፡፡
ሪዞርቱ የገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክት አካል ሲሆን÷ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በጥራት ተገንብቶ ተጠናቋል፡፡
የፕሮጀክቱ ግንባታም የአካባቢው ማኅበረሰብ ነባር የኪነ-ህንፃ ጥበብን ከዘመናዊ የግንባታ ቴክኖሎጂ ጋር በማናበብ ማራኪ በሆነ አግባብ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ነው የተባለው፡፡
ሪዞርቱ በተገነባበት ሥፍራ የሚገኘው የጊቤ ሦስት ኃይል ማመንጫ ሰው ሰራሽ ኃይቅም የሪዞርቱ ተጨማሪ ውበት መሆኑን ተጠቅሷል፡፡
በውስጡም ፕሬዚዳንታዊ የእንግዳ ማረፊያዎች፣ ዘመናዊ መኝታ ክፍሎችና ሌሎች የመዝናኛ ሥፍራዎችን የያዘ ነው፡፡
የሪዞርቱ መገንባትም ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ነው የተጠቆመው፡፡
More Stories
በክልሉ ከተለያዩ መገናኛ ብዙኃን የተውጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን በሚዛን አማን ከተማ አረንጓዴ አሻራ አሳረፉ
የሲዳማ ክልላዊ መንግሥት 5ኛ አመት የምስረታ በዓል በተለያዩ ስነ ስርዓቶች እየተከበረ ነው
በክልሉ በተያዘው የበልግ ወቅት በኩታገጠም ሩዝና በቆሎ እያለሙ ያሉ አርሶአደሮች ተስፋ ሰጪ የሆነ የምርት ውጤት እንድናይ አስችሎናል አሉ።