1ሺህ 446ኛ የኢድ አልፈጥር በዓል ስናከብር ሠላማችንን በማፅናት ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ: መጋቢት 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) 1ሺህ 446ኛ የኢድ አልፈጥር በዓል ስናከብር የተጀመረውን የሠላም ጥረት በማፅናት ሊሆን እንደሚገባ የማረቆ ልዩ ወረዳ አስተዳደር አስታውቋል።
1446ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ በሐይማኖታዊ ስነ ስርዓት በድምቀት ተከብሯል።
የማረቆ ልዩ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ በዚህ ወቅት እንዳሉት፥ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ፆሙን በሶላት፣ በዱኣ እና ለአገራችን ሠላም የበኩሉን አስተዋዕፆ በማድረግ በብዙ ኩነቶች ያሳለፈበት እንደነበር ጠቁመው፥ ዛሬ የበዓሉ ማጠቃለያ በደማቅ ሐይማኖታዊ የተክቢራ ስነ ስርዓት ተካሂዷል ብለዋል።
በዚህ ወር ካከናወናቸው ነገሮች መካከል አንዱ የሠላም ግንባታ ስራችንን በማጽናት በቀጠናችን ላይ የቆየውን የግጭት ሁኔታ በዘላቂነት ለመፍታት መንግስት በጀመረው አግባብ ህዝቡን ደግፎ ሰላሙ እንዲፀና ለማድረግ ጥረት መደረጉን ጠቁመው፥ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከፈጣሪው ጋር የሚገናኝበት ቅዱስ ወር ረመዳን በመሆኑ፥ህዝቡ ሰላሙን በማፅናት ረገድ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ እንደሚገባ አመላክተዋል።
አቶ ከድር መስቀሎ የቢላል መስኪድ ሰብሳቢ በበኩላቸው፥ ረመዳን ፆም ከአሏህ ጋር የምንገናኝበትና የዕዝነት ወር በመሆኑ፥ ምስኪኖችን የምንረዳበት፣ በአንድነት፣ በሠላምና በፍቅር የምናሳልፍበት በዓል ነው ብለዋል።
በማረቆ ልዩ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ሰብሳቢ አቶ ሱሌማን ሰብሮ፥ በዓሉን በመቻቻል፣ ዕርስ በዕርስ በመረዳዳትና ችግረኛ ወገኖቻችንን በማገዝ የዕስልምና አስተምህሮ በሚያዘው መሰረት ሊሆን እንደሚገባ ገልፀው፥ በአጎራባች አከባቢ ከምስራቅ ጉራጌ ዞንና ማረቆ ልዩ ወረዳ የጋራ ኢፍጣር ስነ ስርዓት በማድረግ፥ ፆሙ የሰላም፣ የፍቅር፣ የይቅርታና የአብሮነት መሆኑን በሚያሳይ መልኩ መከናወኑን አስረድተዋል።
በመላው ዓለም በሚገኙ ሙስሊሞች ዘንድ የሚከበረው 1ሺህ 446ኛ የኢድ አልፈጥር በዓል በማረቆ ልዩ ወረዳ ቆሼ ከተማ በድምቀት ሲከበር፥ የልዩ ወረዳው አመራር አካላትና የዕምነቱ ተከታዮች በተገኙበት በሶላት ስነ ስርዓት አክብረዋል።
ዘጋቢ: ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል