የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በዲላ ሁለገብ ስታድየም ተገኝተው ለ1ሺህ 4 መቶ 46ኛው ዒድ አል ፈጥር በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አሰተላለፉ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዲላ ሁለገብ ስታድየም በዓሉ ሲከበር የተገኙት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ለ1 ሺህ 4 መቶ 46ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዓሉን በታላቁ የረመዳን ወቅት ልዩነቶቻችን ሳይገድቡን፣ የኢፍጣር ማዕድ በአብሮነት እንደተቋደስን ሁሉ ለሀገራችን ሰላምና ሁለንተናዊ ብልጽግና ወንድማማችነትን ማጠናከር ይኖርብናል ብለዋል፡፡
የእስልምና እምነት ተከታዮች በረመዳን ፆም ወቅት ያሳዩት የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ እና የአብሮነት እሴቶች ለሀገር ግንባታም የጎላ ፋይዳ እንዳለው የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶክተር መስፍን ደምሴ ገልጸዋል።
የዲላ ከተማን ምቹና ሳቢ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሙስልሙ ማህበረሰብ በልማት ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለመላው ሙስልም ማህበረሰብ የዒድ አል ፈጥር በዓል የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ እና አንድነት እንዲሆንላቸው አስተዳደሪዎቹ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ስነ-ስርዓት ላይ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር)፣ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳይያስ፣ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የዲላ ከተማ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከል በሚደረገው አገራዊ ጥረት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅምና መብት በማስጠበቅ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ