የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በዲላ ሁለገብ ስታድየም ተገኝተው ለ1ሺህ 4 መቶ 46ኛው ዒድ አል ፈጥር በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አሰተላለፉ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዲላ ሁለገብ ስታድየም በዓሉ ሲከበር የተገኙት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ለ1 ሺህ 4 መቶ 46ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዓሉን በታላቁ የረመዳን ወቅት ልዩነቶቻችን ሳይገድቡን፣ የኢፍጣር ማዕድ በአብሮነት እንደተቋደስን ሁሉ ለሀገራችን ሰላምና ሁለንተናዊ ብልጽግና ወንድማማችነትን ማጠናከር ይኖርብናል ብለዋል፡፡
የእስልምና እምነት ተከታዮች በረመዳን ፆም ወቅት ያሳዩት የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ እና የአብሮነት እሴቶች ለሀገር ግንባታም የጎላ ፋይዳ እንዳለው የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶክተር መስፍን ደምሴ ገልጸዋል።
የዲላ ከተማን ምቹና ሳቢ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሙስልሙ ማህበረሰብ በልማት ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለመላው ሙስልም ማህበረሰብ የዒድ አል ፈጥር በዓል የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ እና አንድነት እንዲሆንላቸው አስተዳደሪዎቹ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ስነ-ስርዓት ላይ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር)፣ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳይያስ፣ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የዲላ ከተማ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል