የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በዲላ ሁለገብ ስታድየም ተገኝተው ለ1ሺህ 4 መቶ 46ኛው ዒድ አል ፈጥር በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አሰተላለፉ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 21/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዲላ ሁለገብ ስታድየም በዓሉ ሲከበር የተገኙት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ለ1 ሺህ 4 መቶ 46ኛው የዒድ አል ፈጥር በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በዓሉን በታላቁ የረመዳን ወቅት ልዩነቶቻችን ሳይገድቡን፣ የኢፍጣር ማዕድ በአብሮነት እንደተቋደስን ሁሉ ለሀገራችን ሰላምና ሁለንተናዊ ብልጽግና ወንድማማችነትን ማጠናከር ይኖርብናል ብለዋል፡፡
የእስልምና እምነት ተከታዮች በረመዳን ፆም ወቅት ያሳዩት የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ እና የአብሮነት እሴቶች ለሀገር ግንባታም የጎላ ፋይዳ እንዳለው የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶክተር መስፍን ደምሴ ገልጸዋል።
የዲላ ከተማን ምቹና ሳቢ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሙስልሙ ማህበረሰብ በልማት ሥራዎች ላይ በመሳተፍ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለመላው ሙስልም ማህበረሰብ የዒድ አል ፈጥር በዓል የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ እና አንድነት እንዲሆንላቸው አስተዳደሪዎቹ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ስነ-ስርዓት ላይ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር)፣ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አበባየሁ ኢሳይያስ፣ የዲላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የዲላ ከተማ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ