የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሀላባ ዞን እየተከበረ ነው
1446ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ በሚገኘው የኢድ አደባባይ የእስልምና እምነት ተከታዮች በተገኙበት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
በረመዳን ወር የታየውን አብሮነትና መተሳሰብ በማስቀጠል እና ለተቸገሩ በማገዝ ይህን የዒድ አል-ፈጥር በዓል ማክበር እንደሚገባም ተገልጿል።
በበዓሉም በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር መሀመድ ኑሪዬን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ የእምነቱ ተከታዮች በዓሉን እያከበሩ ይገኛሉ።
በዚህም የዒድ ሶላት ሥነ-ሥርዓት እና ሌሎች ሀይማኖታዊ ተግባራት በመካሄድ ላይ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ቃለአብ ፀጋዬ

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ