የ1 ሺህ 4 መቶ 46ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በጌዴኦ ዞን ዲላ ሁለገብ ስታዲየም በድምቀት እየተከበረ ነው
የጌዴኦ ዞን እስልምና እምነት አባቶችም ለዒድ አል ፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በማስተላለፍ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
1 ሺህ 4መቶ 46ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓልን የእምነቱ ተከታዮች በሶላት፣ ቴክብራ በስግደትና በተለያዩ ኃይማኖታዊ ክዋኔዎች በዲላ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም በድምቀት በማክበር ለይ ናቸው።
ከእስልምና እምነት አባቶች የተለያዩ ኃይማኖታዊ መልዕክቶች ስለ ኢድ አል ፈጥር በዓል እያስተላላፉ ነው።
የኢድ አል-ፈጥር በዓል በመላው ዓለም በሚገኙ ሙስሊሞች ከሚከበሩት በዓላት አንዱ ሲሆን የተከበረው የረመዳን ወር የፆም፣ የፀሎት እና የዕዝነት እንዲሁም የአላህን ምህረት እየተማጸኑ ያሳለፉበት ወር መሆኑ ይታወሳል።
ህዝበ ሙስልሙ በዓሉን ሲያከበር የተቸገሩትን፣ አቅመ ደካሞችን እና ጎረቤቶቻቸውን በማሰብ መሆን እንደለበት ተገልጿል።
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የአንድነትና የአብሮነት እንዲሆንላቸው የኃይማኖት አባቶቹ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የሴቶች የልማት ህብረትን በማጠናከር የሴቶችን ተጠቃሚነት በይበልጥ ማረጋገጥ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ