የ1 ሺህ 4 መቶ 46ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በጌዴኦ ዞን ዲላ ሁለገብ ስታዲየም በድምቀት እየተከበረ ነው
የጌዴኦ ዞን እስልምና እምነት አባቶችም ለዒድ አል ፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በማስተላለፍ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
1 ሺህ 4መቶ 46ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓልን የእምነቱ ተከታዮች በሶላት፣ ቴክብራ በስግደትና በተለያዩ ኃይማኖታዊ ክዋኔዎች በዲላ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም በድምቀት በማክበር ለይ ናቸው።
ከእስልምና እምነት አባቶች የተለያዩ ኃይማኖታዊ መልዕክቶች ስለ ኢድ አል ፈጥር በዓል እያስተላላፉ ነው።
የኢድ አል-ፈጥር በዓል በመላው ዓለም በሚገኙ ሙስሊሞች ከሚከበሩት በዓላት አንዱ ሲሆን የተከበረው የረመዳን ወር የፆም፣ የፀሎት እና የዕዝነት እንዲሁም የአላህን ምህረት እየተማጸኑ ያሳለፉበት ወር መሆኑ ይታወሳል።
ህዝበ ሙስልሙ በዓሉን ሲያከበር የተቸገሩትን፣ አቅመ ደካሞችን እና ጎረቤቶቻቸውን በማሰብ መሆን እንደለበት ተገልጿል።
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የአንድነትና የአብሮነት እንዲሆንላቸው የኃይማኖት አባቶቹ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ