የ1 ሺህ 4 መቶ 46ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በጌዴኦ ዞን ዲላ ሁለገብ ስታዲየም በድምቀት እየተከበረ ነው
የጌዴኦ ዞን እስልምና እምነት አባቶችም ለዒድ አል ፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በማስተላለፍ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
1 ሺህ 4መቶ 46ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓልን የእምነቱ ተከታዮች በሶላት፣ ቴክብራ በስግደትና በተለያዩ ኃይማኖታዊ ክዋኔዎች በዲላ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም በድምቀት በማክበር ለይ ናቸው።
ከእስልምና እምነት አባቶች የተለያዩ ኃይማኖታዊ መልዕክቶች ስለ ኢድ አል ፈጥር በዓል እያስተላላፉ ነው።
የኢድ አል-ፈጥር በዓል በመላው ዓለም በሚገኙ ሙስሊሞች ከሚከበሩት በዓላት አንዱ ሲሆን የተከበረው የረመዳን ወር የፆም፣ የፀሎት እና የዕዝነት እንዲሁም የአላህን ምህረት እየተማጸኑ ያሳለፉበት ወር መሆኑ ይታወሳል።
ህዝበ ሙስልሙ በዓሉን ሲያከበር የተቸገሩትን፣ አቅመ ደካሞችን እና ጎረቤቶቻቸውን በማሰብ መሆን እንደለበት ተገልጿል።
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የአንድነትና የአብሮነት እንዲሆንላቸው የኃይማኖት አባቶቹ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል