የ1 ሺህ 4 መቶ 46ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በጌዴኦ ዞን ዲላ ሁለገብ ስታዲየም በድምቀት እየተከበረ ነው
የጌዴኦ ዞን እስልምና እምነት አባቶችም ለዒድ አል ፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በማስተላለፍ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
1 ሺህ 4መቶ 46ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓልን የእምነቱ ተከታዮች በሶላት፣ ቴክብራ በስግደትና በተለያዩ ኃይማኖታዊ ክዋኔዎች በዲላ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም በድምቀት በማክበር ለይ ናቸው።
ከእስልምና እምነት አባቶች የተለያዩ ኃይማኖታዊ መልዕክቶች ስለ ኢድ አል ፈጥር በዓል እያስተላላፉ ነው።
የኢድ አል-ፈጥር በዓል በመላው ዓለም በሚገኙ ሙስሊሞች ከሚከበሩት በዓላት አንዱ ሲሆን የተከበረው የረመዳን ወር የፆም፣ የፀሎት እና የዕዝነት እንዲሁም የአላህን ምህረት እየተማጸኑ ያሳለፉበት ወር መሆኑ ይታወሳል።
ህዝበ ሙስልሙ በዓሉን ሲያከበር የተቸገሩትን፣ አቅመ ደካሞችን እና ጎረቤቶቻቸውን በማሰብ መሆን እንደለበት ተገልጿል።
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የአንድነትና የአብሮነት እንዲሆንላቸው የኃይማኖት አባቶቹ መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።
ዘጋቢ፡ ተስፋዬ ጎበና – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ