በልዩ ወረዳዉ የመጋቢታዊያን ቀን በማስመልክት “ትላንት፣ ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና” በሚል መሪ ቃል በወልቂጤ ከተማ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተደረገ።
በዚህ ወቅት የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ምስጋናዉ ማትዮስ እንደገለፁት በአገር አቀፍ ደረጃ በመጋቢት ወር በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል።
በተለይም የህብረተሰቡን ልማታዊ ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ የሚችሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ስራ ላይ የዋሉበት ወር መሆኑንም ገልፀዋል።
የቀቤና ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞሳ ኢዶሳ በበኩላቸዉ መጋቢት ወር የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚንስትር ደ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ስልጣን የመጡበትና በአገር አቀፍ ብሎም በልዩ ወረዳው የህብረተሰቡ የመልማት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት ወር መሆኑንም ገልፀዋል።
ይህንን በማስቀጠል ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባም አክለዋል።
የቀቤና ልዩ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አቡበክር ዱላ የመጋቢት ወር ድሎችን ማስቀጠል እንደሚገባና በተለይም ወጣቱ ትዉልድ አብሮነትንና የአከባቢዉን ሰላም ማስጠበቅ እንዳለበት ተናግረዋል።
የልዩ ወረዳዉ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጁሃር ጀማል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የህብረተሰቡን በተለይ የወጣቱን ጤና ሰላም እና አንድነት ለማስጠበቅ ያለዉ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ፕሮግራሙ ወጣቶች ራሳቸውን ከሱስ በመጠበቅ ጤናማና ንቁ እንዲሆኑ የሚያስችላው ከመሆኑም በሻገር እርስ በራሳቸው ያላቸውን ግንኙነት እንዲያጠናክሩና ለአካባቢያቸውና ለሀገራቸው ሰላም መጠበቅ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ የሚያግዛቸው መሆኑን የፕሮግራሙ ተሳታፊ ወጣቶች ተናግረዋል ፡፡
በመሆኑም መሰል የጋራ ስፖርት ፕሮግራሞች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ገልፀዋል ፡፡
በአካል ብቃት እንቅስቃሴዉ የክልሉ የስራ ሀላፊዎች፣ የልዩ ወረዳዉ አመራሮች፣ ወጣቶችና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ ፡በሪያድ ሙህዲን-ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሳውላ ካምፓስ ለ9ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 121 ተማሪዎችን አስመረቀ
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ