ስምምነቱ በመንግስትና በግሉ ዘርፍ ያላቸውን ቁርኝት እንደሚያጠናክር ተመላክቷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን እንገለፁት፤ የግብ ስምምነቱ በዋናነት የምክክር መድረኮችን ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር በመፍጠር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የአሰራር ማቀፍ በማስፈለጉ ነው።
የግሉ ዘርፍ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ላይ የላቀ አበርክቶ እንዲኖረው አቅዶ እየሰራ በመሆኑ ዘርፉ በየደረጃው በምክር ቤት ተደራጅቶ የሚንቀሳቀስበትና ለላቀ ውጤት የሚበቃበት አካሄድ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ክልሉ ባለ ብዙ ፀጋ ባለቤት እንደመሆኑ መጠን ይህንን ፀጋ ለሚመለከታቸው አካላት አጉልቶ በማሳየት ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ አልሚዎች የማስተዋወቅና ኢንቨስተሮችን ወደ ክልላችን የመጋበዝ ሃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድ ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቦጋለ ቢታኔ በበኩላቸው፤ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ የጋራ ምክክር የሚያደርግበትና በሁሉም መዋቅሮች ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት የግብ ስምምነት እንደተፈራረሙ አስረድተዋል።
ንግድና ኢንቨስትመትን ማሳለጥ ዋና አላማው ያደረገው ንግድና ዘርፍ ምክር ቤቱ ሀገሪቱ የምትፈልገውን ልማት ለማሳካት የሚያስችል መሰረት መሆኑን አስታውቀዋል አቶ ቦጋለ።
በመንግስትና በንግዱ ዘርፍ እንደ ድልድይ ሆኖ እያገለገለ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ መንግስት ከንግዱ ማህበረሰብ የሚፈልገውን መረጃ በመውሰድ ችግሮችን እንዲፈቱ በማድረግና ሁሉም ነጋዴ ሰላማዊ የሆነ የንግድ ስርአት እንዲኖር ማስቻል ነው ብለዋል።
በክልሉ ከ1መቶ 48ሺ በላይ ነጋዴዎች መኖራቸውን ገልፀው ሁሉም ነጋዴ ወደ ተቋሙ በመምጣት ችግሮችን በጋራ እንዲፈቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ