ስምምነቱ በመንግስትና በግሉ ዘርፍ ያላቸውን ቁርኝት እንደሚያጠናክር ተመላክቷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን እንገለፁት፤ የግብ ስምምነቱ በዋናነት የምክክር መድረኮችን ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር በመፍጠር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የአሰራር ማቀፍ በማስፈለጉ ነው።
የግሉ ዘርፍ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ላይ የላቀ አበርክቶ እንዲኖረው አቅዶ እየሰራ በመሆኑ ዘርፉ በየደረጃው በምክር ቤት ተደራጅቶ የሚንቀሳቀስበትና ለላቀ ውጤት የሚበቃበት አካሄድ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ክልሉ ባለ ብዙ ፀጋ ባለቤት እንደመሆኑ መጠን ይህንን ፀጋ ለሚመለከታቸው አካላት አጉልቶ በማሳየት ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ አልሚዎች የማስተዋወቅና ኢንቨስተሮችን ወደ ክልላችን የመጋበዝ ሃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድ ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቦጋለ ቢታኔ በበኩላቸው፤ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ የጋራ ምክክር የሚያደርግበትና በሁሉም መዋቅሮች ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት የግብ ስምምነት እንደተፈራረሙ አስረድተዋል።
ንግድና ኢንቨስትመትን ማሳለጥ ዋና አላማው ያደረገው ንግድና ዘርፍ ምክር ቤቱ ሀገሪቱ የምትፈልገውን ልማት ለማሳካት የሚያስችል መሰረት መሆኑን አስታውቀዋል አቶ ቦጋለ።
በመንግስትና በንግዱ ዘርፍ እንደ ድልድይ ሆኖ እያገለገለ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ መንግስት ከንግዱ ማህበረሰብ የሚፈልገውን መረጃ በመውሰድ ችግሮችን እንዲፈቱ በማድረግና ሁሉም ነጋዴ ሰላማዊ የሆነ የንግድ ስርአት እንዲኖር ማስቻል ነው ብለዋል።
በክልሉ ከ1መቶ 48ሺ በላይ ነጋዴዎች መኖራቸውን ገልፀው ሁሉም ነጋዴ ወደ ተቋሙ በመምጣት ችግሮችን በጋራ እንዲፈቱ ጥሪ አቅርበዋል።
ዘጋቢ፡ ገነት መኮንን – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ