የኢድ አል ፈጥር በዓል ያለምንም የጸጥታ ስጋት በድምቀት እንዲከበር በቂ ዝግጅት መደረጉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ
ኮሚሽኑ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1ሺህ 446ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክትም አስተላልፏል ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና የወንጀል መከላከልና ትራፊክ ዘርፍ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር አብረሃም ቲርካሶ እንዳሉት በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የኢድ አል ፈጥር በዓል በአደባባይ በድምቀት የሚከበር በመሆኑ በዓሉን ያለምንም ጸጥታ ስጋት ማክበር እንዲቻል በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች በቂ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል ።
የክልሉ ፖሊስ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከሌሎች የጸጥታ አካላት ጋረ በጋራ እየሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል ።
በዓሉን ለማክበር በሚያደርገው በማንኛውም እንቅስቃሴ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም ገልጸዋል ።
በተለይም ከእሳትና ከኤሌክትሪክ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማደረግ እንደሚገባም ምክትል ኮሚሽነሩ አሳስበዋል ።
ዘጋቢ :ታምራት አለሙ -ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ