ከስራ አጥነት ተነስተው ስራ እድል ፈጠራን ቢዝነስ በማድረግ ተጠቃሚ መሆናቸውን የክልሉ ወጣቶች ተናግረዋል።
ስራ አጥ ዜጎች የስራ እድል ተጠቃሚና በስራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ በሚደረገው ሁሉ አቀፍ እንቅስቃሴ ውስጥ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን በሁሉም ዘርፎች ያሉ እድሎችን አሟጦ በመጠቀም የክልሉ ዜጎች የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
እነዚህ በክልሉ በተለያዩ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ላይ የተደራጁ ወጣቶች በተሰማሩበት ዘርፍ ከራሳቸው ባለፈ ለሀገር ኢኮኖሚ አበርክቷቸው ከፍ ያለ እንደሆነና መንግስት እንደ ሀገር ትርጉም ባለው ደረጃ የስራ አጥነትን ችግር ለመቀነስ እያደረገ ያለው ጥረት ይበል የሚያሰኝና ሊጠናከር የሚገባ ስለመሆኑም የክልሉ ወጣቶች ገልፀዋል።
ክልሉ በሁሉም ዘርፎች ያሉ እድሎችን በመጠቀም ዜጎች የስራ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማድረጉ ተግባር በተጠናከረ መልኩ እየተሰራበት ሲሆን ለ350 ሺህ ስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን የገለፁት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሠረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ መሐመድ ኑሪዬ(ዶ/ር) ናቸው።
ዘጋቢ፡ ቴዎድሮስ ወርቅነህ

More Stories
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ እና የአደረጃጀት ዘርፍ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዕቅድ ዙሪያ በታርጫ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ነው
ኦሞ ባንክ ሳውላ ዲስትሪክት በ2018 በጀት ዓመት ከ86 ሚሊዮን ብር በላይ የተጣራ ቁጠባ ማስመዝገቡን ገለጸ
እየተካሔደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሀገሪቱ አንድነት እና ሠላም ለማስፈን ፋይዳው የጎላ መሆኑን የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ