በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮሬ እና ቡርጂ ዞኖች አዋሳኝ አካባቢዎች ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በዘላቂ ሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ጎአ፣ የ37ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ካሳዬ ተገኝ፣ የኮሬ ዞን፣ የምዕራብ ጉጂ ዞንና የቡርጂ ዞን አስተባባሪዎችና የፀጥታ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሮችን በማስፈን በአካባቢው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እንደሆነም ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተሾመ ፀጋዬ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ