በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮሬ እና ቡርጂ ዞኖች አዋሳኝ አካባቢዎች ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በዘላቂ ሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ጎአ፣ የ37ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ካሳዬ ተገኝ፣ የኮሬ ዞን፣ የምዕራብ ጉጂ ዞንና የቡርጂ ዞን አስተባባሪዎችና የፀጥታ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሮችን በማስፈን በአካባቢው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እንደሆነም ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተሾመ ፀጋዬ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የሴቶች የልማት ህብረትን በማጠናከር የሴቶችን ተጠቃሚነት በይበልጥ ማረጋገጥ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ