በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮሬ እና ቡርጂ ዞኖች አዋሳኝ አካባቢዎች ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በዘላቂ ሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ጎአ፣ የ37ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ካሳዬ ተገኝ፣ የኮሬ ዞን፣ የምዕራብ ጉጂ ዞንና የቡርጂ ዞን አስተባባሪዎችና የፀጥታ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሮችን በማስፈን በአካባቢው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እንደሆነም ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተሾመ ፀጋዬ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከል በሚደረገው አገራዊ ጥረት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅምና መብት በማስጠበቅ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ