በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮሬ እና ቡርጂ ዞኖች አዋሳኝ አካባቢዎች ወቅታዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በዘላቂ ሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው
በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ጎአ፣ የ37ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ካሳዬ ተገኝ፣ የኮሬ ዞን፣ የምዕራብ ጉጂ ዞንና የቡርጂ ዞን አስተባባሪዎችና የፀጥታ አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስተጋብሮችን በማስፈን በአካባቢው ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እንደሆነም ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተሾመ ፀጋዬ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ