የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር የሚያጠናክሩ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን በጌዴኦ ዞን የገደብ ወረዳ አስተዳደር ገለጸ
ወረዳውን ከአጎራባች ወረዳዎችና አዋሳኝ ክልል ጋር የሚያገናኝ የመንገድ ጥገና ሥራ በተጀመረበት ወቅት የገደብ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ምትኩ እንደገለጹት በወረዳው በሚገኙ 13 ቀበሌያት የመንገድ ችግር መኖሩን ጠቅሰው ይሄን ለመቅረፍም እየተሰራ ነው፡፡
የተጀመረው የመንገድ ጥገና ሐርሙፎ-ሺፎ ኮቾሬ ወረዳን ከወረዳው ጋር ከማገናኘት ባለፈ የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ያጠናክራል ያሉት የወረዳው አስተዳዳሪ፣ አርሶአደሩ ያመረተውን ምርት ወደ ገበያ ለማውጣትና ወደ ህክምና ተቋም ለመሄድ የነበረውን ችግር እንደሚቀርፍ ተናግረዋል።
መንገዱ ከፍተኛ ችግር የነበረበት ቢሆንም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ አስተዳዳሪው ገልጸዋል።
በገደብ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ሽፈራው ወረዳውን ከአጎራባች ወረዳዎችና ኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ቀበሌዎች ጋር የሚያገናኙ መንገዶች በወረዳው ከሚሠሩት ባለፈ፣ ከገደብ ሐርሙፎ-ሺፎ ኮቾሬ ወረዳን የሚያገናኝ 17 ኪ.ሜ የጥገና መንገድ ማስጀመራቸውን ተናግረዋል።
ለበርካታ ጊዜያት የመንገድ ጥገናው እንዲደረግላቸው ሲጠይቁ ከነበሩት የአከባቢው ነዋሪዎችም መንገዱ መሠራቱ ወደ ህክምና ተቋማት ለመሄድና የንግድ ሥራ እንቅስቃሴን ያለችግር ለማከናወን እንደሚረዳ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡- ውብሸት ካሣሁን – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል