ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 13 ሚሊየን ብር ድጋፍ እንደሚያደርግ በጋሞ ዞን የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት አስታወቀ
ሀዋሳ፡ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በሚደረገው ሂደት 13 ሚሊየን ብር ድጋፍ እንደሚያደርግ በጋሞ ዞን የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡
የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋንጫውን ከአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ተረክቧል።
የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋንጫ ለአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ባስረከቡበት ወቅት የአርባምንጭ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ ሊዲያ ካንቲባ እንደተናገሩት፤ በትውልድ ቅብብሎሽ ሀገርን አጽንተው እንዳቆዩ አርበኛ አያቶቻችን ዛሬም ትውልዱ ለህዳሴ ግድብ ግንባታ አሻራውን በማሳረፍ የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ እያደረገ ይገኛል።
አክለውም የቀደመ ማንነታችንን በማሳየት ብሔራዊ ኩራታችን የሆነው ግድባችን እንዲጠናቀቅ ሌት ከቀን በመረባረባችንና በመተጋገዛችን ለገጠመን ጠላታችን ሳንበገር የሀገር ክብር የሆነውን ማሳየት ችለናል ነው ያሉት።
የአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አለማየሁ ዘይቴ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከውጭ ጫና ተላቆ የግንባታ ሂደቱ 97 በመቶ በመድረሱ ታላቅ ኩራት ይሰማናል።
እንደ ከዚህ ቀደም የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር በስጦታ፣ በቦንድ ግዢና በዓይነት አሁን የተሰጠውን 13 ሚሊየን ብር ድጋፍ ለማድረግ ገቢ የማሳባሰቡ ሥራ መጀመሩን ገልጸዋል።
በደማቅ አቀባበል የኢትዮጵያ ህዳሴ ዋንጫ የተረከበው የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት የተሰጠውን ኮታ በአግባቡ በመፈጸም ለምዕራብ ዓባያ ወረዳ ለማስረከብ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል።
ከአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ነዋሪዎች መካከል ያነጋገርናቸው በሰጡን አስተያየት ከዚህ ቀደም በስጦታ፣ በቦንድ ግዥና በዓይነት ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰው አሁንም ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ድጋፍ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ: ሰለሞን አላሶ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ