በወልቂጤ ከተማ የተፈጠረውን ሰላም በዘላቂነት ለማፅናት የህዝቦችን አብሮነትና አንድነት ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ
ሀዋሳ: መጋቢት 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በወልቂጤ ከተማ የተፈጠረውን ሰላም በዘላቂነት ለማፅናት የህዝቦችን አብሮነትና አንድነት ማጠናከር እና የህዝብ ለህዝብ ተስስር እንዲዳብር እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።
በከተማው ለግጭት ምክንያት የነበሩ ችግሮችን በመለየት የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት እየሰሩ መሆናቸው ደግሞ በከተማው ሰላም እንዲሰፍን አድርጓል ሲሉ ነዋሪዎች ገልፀዋል።
ሰላምን በሰላሙ ጊዜ መስራት ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም የግጭት ችግሮችንና አዝማሚያዎችን በመረዳት የሰላም ባህልንም ለመገንባት ሚናው የጎላ ነው። ታዲያ ይህንን የተረዱ የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች ለሰላማቸው ዘብ በመቆምና አለመግባባቶችን በመፍታት ከተማቸው ሰላም መሆኗን ተናግረዋል።
በከተማው ዘላቂ ሰላም ለማስፈንና የህዝቦችን አንድነትና አብሮነት በማጠናከር የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሀገር በቀል የግጭት አፈታት ዘዴ በመፍታት የህዝብ ለህዝብ ትስስር እንዲዳብር እየተሰራ መሆኑን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር ተናግረዋል።
በከተማው ለግጭት ምክንያት የነበሩ ችግሮችንም በዘላቂነት ለመፍታት የክልል መንግስት ከፌደራል መንግስት ጋር በመቀናጀት የጥናት ቡድን ተዋቅሮ እየተሰራ ስለመሆኑም ከንቲባው አስረድተዋል።
በክልሉ ህዝቦች የተሟላ ሰላምና ልማት እንዳያረጋግጡ ከፋፋይ ትርክቶችን በማሰራጨት ህገ ወጥ ተግባር በሚሰሩ አካላት ላይ ክልሉ ህጋዊ እርምጃ በመውሰዱ ሰላምን ማፅናት ተችሏል ያሉት ደግሞ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መሐመድ ኑሪዬ ናቸው።
ዘጋቢ: ቴድሮስ ወርቅነህ

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል