ሀዋሳ፡ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዱራሜ ክላስተር “ትላንት ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና የመጋቢታዊያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ የተካሄደ ነው።
በውይይት መድረኩም በዱራሜ ክላስተር የሚገኙ የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደንና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃም መጫ፤ ባለፉት የለውጥ አመታት በተለያዩ ዘርፎች በርካታ ተግባራት መተግበራቸውን አንስተው ይህ መድረክም እነዚህ ለውጦች የሚነሱበትና የቤት ስራ በሚጠይቁ ተግባራት ላይም በቁጭት ለመስራት እንዲያስችል የተዘጋጀ ነው ብለዋል።
ብልፅግና ፓርቲ ሀገርን ወደ ሁለንተናዊ እድገት ለማሻገር እንዲሁም ሁሉም በእኩልነት የሚሳተፍበትን ስርአት ከመዘርጋት ጀምሮ የሚታዩ ውጤቶችን ማስመዝገቡን የተናገሩት ኃላፊው፤ በዚህም የጥላቻ ግንብን በማፍረስና ብሄራዊ ትርክትን በመገንባት ሀገር የገጠማትን ፈተና በድል እድትሻገር የሚያስችሉ ስራዎችም በትኩረት ስለመተግበራቸው አንስተዋል።
ዘላቂ ሰላምን ማስፈን፣ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሻገር እንዲሁም ዲፕሎማሲ ስራዎችን ማጠናከርና ሀገር በአለም አቀፍ መድረኮች ተሰሚነቷ እንዲጨምር ማድረግ በለውጡ አመታት በትኩረት የተተገበሩ ስራዎች መሆናቸውንም ኃላፊው ተናግረዋል።
እንደ ሀገር ብሎም እንደ ክልል የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራትን ለማስቀጠልና አሁንም ህዝብን የሚፈትኑ ተግባራትን ለማስተካከል ሁሉም በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባውም ኃላፊው በመልእክታቸው አሳስበዋል።
በውይይት መድረኩ በለውጡ አመታት የተከናወኑ ተግባራትና ቀጣይ የቤት ስራዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።
ዘጋቢ፡ ቃለአብ ፀጋዬ

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ