ሀዋሳ፡ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዱራሜ ክላስተር “ትላንት ዛሬና ነገን ለኢትዮጵያ ልዕልና የመጋቢታዊያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ የተካሄደ ነው።
በውይይት መድረኩም በዱራሜ ክላስተር የሚገኙ የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ደንና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብርሃም መጫ፤ ባለፉት የለውጥ አመታት በተለያዩ ዘርፎች በርካታ ተግባራት መተግበራቸውን አንስተው ይህ መድረክም እነዚህ ለውጦች የሚነሱበትና የቤት ስራ በሚጠይቁ ተግባራት ላይም በቁጭት ለመስራት እንዲያስችል የተዘጋጀ ነው ብለዋል።
ብልፅግና ፓርቲ ሀገርን ወደ ሁለንተናዊ እድገት ለማሻገር እንዲሁም ሁሉም በእኩልነት የሚሳተፍበትን ስርአት ከመዘርጋት ጀምሮ የሚታዩ ውጤቶችን ማስመዝገቡን የተናገሩት ኃላፊው፤ በዚህም የጥላቻ ግንብን በማፍረስና ብሄራዊ ትርክትን በመገንባት ሀገር የገጠማትን ፈተና በድል እድትሻገር የሚያስችሉ ስራዎችም በትኩረት ስለመተግበራቸው አንስተዋል።
ዘላቂ ሰላምን ማስፈን፣ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት መሻገር እንዲሁም ዲፕሎማሲ ስራዎችን ማጠናከርና ሀገር በአለም አቀፍ መድረኮች ተሰሚነቷ እንዲጨምር ማድረግ በለውጡ አመታት በትኩረት የተተገበሩ ስራዎች መሆናቸውንም ኃላፊው ተናግረዋል።
እንደ ሀገር ብሎም እንደ ክልል የተጀመሩ ውጤታማ ተግባራትን ለማስቀጠልና አሁንም ህዝብን የሚፈትኑ ተግባራትን ለማስተካከል ሁሉም በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባውም ኃላፊው በመልእክታቸው አሳስበዋል።
በውይይት መድረኩ በለውጡ አመታት የተከናወኑ ተግባራትና ቀጣይ የቤት ስራዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።
ዘጋቢ፡ ቃለአብ ፀጋዬ

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጂንካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ23ኛ ዙር በተለያዩ የሙያ መስኮች በመደበኛና በማታ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 347 ተማሪዎችን አስመረቀ
በ2018 በጀት ዓመት የተቀመጡ ግቦችን በማሳካት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል – አቶ ፍቅሬ አማን
ሚዲያን ለአዎንታዊ ነገር በመጠቀም ወጣቱ ሀገርን መገንባት አለበት – የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን