በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን ከቃል እስከ ባሕል በሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔ አቅጣጫዎች ላይ የወጣቶች ክንፍ ሚናን በተመለከተ የምክክር መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሂዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ወጣት አስቻለው መሸሻ፤ በክልሉ በሁሉም አካባቢ የሚደረገውን የወጣቶች ክንፍ መድረክ ዓላማን አስረድተዋል።
የአሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ ለወጣቶች ባስተላለፉት መልክት፤ ወጣቱ ሕብረብሔራዊነት እና ገዥ ትርክትን በማጠናከር ለአንድነትና ለሀገር ግንባታ የድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።
አቶ ጉራልቅ አክለውም በዞኑ ያሉ ፀጋዎችንና ዕድሎችን በመጠቀም ፓርቲው የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
የዞኑ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ገበየሁ በበኩላቸው፤ ፓርቲው የወጣቱ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎችና አቅጣጫዎችን ለታዳሚው በሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ለተግባራዊነቱ ሁሉም በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ በውይይት መድረኩ የተሳተፉ ወጣቶች አንስተዋል።
በዞኑ ያሉ ሁሉንም ወጣቶች ተደራሽ ለማድረግ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ተመሳሳይ መድረኮችን በማዘጋጀት የወጣቱ እኩል ተሳታፊነትንና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚሠራም በውይይቱ ማጠቃለያ ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የፍትህ ተቋማት ተገልጋዩን ህብረተሰብ በሚመጥን መልኩ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ገለፁ
በተገልጋይ እርካታና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ጥምረት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ
የዜጎችን ህይወት በማቀራረብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሚረዱ ጉዳዮች አንዱ የበጎ ፈቃድ ሥራ መሆኑ ተጠቆመ