በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን ከቃል እስከ ባሕል በሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔ አቅጣጫዎች ላይ የወጣቶች ክንፍ ሚናን በተመለከተ የምክክር መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሂዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ወጣት አስቻለው መሸሻ፤ በክልሉ በሁሉም አካባቢ የሚደረገውን የወጣቶች ክንፍ መድረክ ዓላማን አስረድተዋል።
የአሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ ለወጣቶች ባስተላለፉት መልክት፤ ወጣቱ ሕብረብሔራዊነት እና ገዥ ትርክትን በማጠናከር ለአንድነትና ለሀገር ግንባታ የድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።
አቶ ጉራልቅ አክለውም በዞኑ ያሉ ፀጋዎችንና ዕድሎችን በመጠቀም ፓርቲው የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
የዞኑ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ገበየሁ በበኩላቸው፤ ፓርቲው የወጣቱ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎችና አቅጣጫዎችን ለታዳሚው በሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ለተግባራዊነቱ ሁሉም በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ በውይይት መድረኩ የተሳተፉ ወጣቶች አንስተዋል።
በዞኑ ያሉ ሁሉንም ወጣቶች ተደራሽ ለማድረግ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ተመሳሳይ መድረኮችን በማዘጋጀት የወጣቱ እኩል ተሳታፊነትንና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚሠራም በውይይቱ ማጠቃለያ ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የፀረ-ተህዋስያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን ለመከላከል በሚደረገው አገራዊ ጥረት ውስጥ የሚዲያ ባለሙያዎች ግንባር ቀደም ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ
መምህራን የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅምና መብት በማስጠበቅ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መምህራን ማህበር አስታወቀ
የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራትን ለማፋጠን ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ታክስ በወቅቱና በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገለጸ