በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን ከቃል እስከ ባሕል በሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔ አቅጣጫዎች ላይ የወጣቶች ክንፍ ሚናን በተመለከተ የምክክር መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሂዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ወጣት አስቻለው መሸሻ፤ በክልሉ በሁሉም አካባቢ የሚደረገውን የወጣቶች ክንፍ መድረክ ዓላማን አስረድተዋል።
የአሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ ለወጣቶች ባስተላለፉት መልክት፤ ወጣቱ ሕብረብሔራዊነት እና ገዥ ትርክትን በማጠናከር ለአንድነትና ለሀገር ግንባታ የድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።
አቶ ጉራልቅ አክለውም በዞኑ ያሉ ፀጋዎችንና ዕድሎችን በመጠቀም ፓርቲው የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
የዞኑ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ገበየሁ በበኩላቸው፤ ፓርቲው የወጣቱ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎችና አቅጣጫዎችን ለታዳሚው በሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ለተግባራዊነቱ ሁሉም በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ በውይይት መድረኩ የተሳተፉ ወጣቶች አንስተዋል።
በዞኑ ያሉ ሁሉንም ወጣቶች ተደራሽ ለማድረግ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ተመሳሳይ መድረኮችን በማዘጋጀት የወጣቱ እኩል ተሳታፊነትንና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚሠራም በውይይቱ ማጠቃለያ ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የሴቶች የልማት ህብረትን በማጠናከር የሴቶችን ተጠቃሚነት በይበልጥ ማረጋገጥ ይገባል – ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በግብርናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እንደሚሰራ የጋሞ ዞን አሰተዳደር አሰታወቀ
በሀሳብ ልዕልና የሚያምን የፖለቲካ ሥነ-ምህዳርን በማስፋት ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በመመካከርና በመደጋገፍ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ