በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአሪ ዞን ከቃል እስከ ባሕል በሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ውሳኔ አቅጣጫዎች ላይ የወጣቶች ክንፍ ሚናን በተመለከተ የምክክር መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሂዷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ወጣት አስቻለው መሸሻ፤ በክልሉ በሁሉም አካባቢ የሚደረገውን የወጣቶች ክንፍ መድረክ ዓላማን አስረድተዋል።
የአሪ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጉራልቅ ይዥማልቅ ለወጣቶች ባስተላለፉት መልክት፤ ወጣቱ ሕብረብሔራዊነት እና ገዥ ትርክትን በማጠናከር ለአንድነትና ለሀገር ግንባታ የድርሻቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።
አቶ ጉራልቅ አክለውም በዞኑ ያሉ ፀጋዎችንና ዕድሎችን በመጠቀም ፓርቲው የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
የዞኑ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ ገበየሁ በበኩላቸው፤ ፓርቲው የወጣቱ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎችና አቅጣጫዎችን ለታዳሚው በሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ለተግባራዊነቱ ሁሉም በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ በውይይት መድረኩ የተሳተፉ ወጣቶች አንስተዋል።
በዞኑ ያሉ ሁሉንም ወጣቶች ተደራሽ ለማድረግ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ተመሳሳይ መድረኮችን በማዘጋጀት የወጣቱ እኩል ተሳታፊነትንና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚሠራም በውይይቱ ማጠቃለያ ተገልጿል።
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የግል እና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን በተገቢው በመጠቀም ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የእኖር ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት አስገነዘበ
12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በተቋማት የድርጊት መርሐ-ግብርና በፀደቀላቸው በጀት መሠረት ማሰራጨቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡኢ ከተማ አስተዳደር እየተገነባ የሚገኘውን ብሉ ኤለፋንት ፋይበር ቦርድ ካምፓኒ ጎበኙ