ከ200 የሚበልጡ የኢትዮጵያ ከተሞች ከንቲባዎች በአዲስ አበባ የለውጡን ስኬት ማሳያ የሆኑ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን መጎብኘታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትሰሰር ገጻቸው “ከ200 በላይ ለሚሆኑ የኢትዮጵያ ከተሞች ከንቲባዎች በመዲናዋ ከለውጡ ወዲህ አቅደን በመፈፀም ያስገኘናቸውን ስኬቶችንና ውጤታችንን ያሳዩ ታላላቅ ፕሮጀክቶችን እንዲሁም ሰው ተኮር ስራዎቻችንን አስጎብኝተናል” ብለዋል።
በመቀጠልም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር የበለፀጉ ከተሞችን ለመፍጠር ከንቲባዎች በሚጫወቱት ሚና ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገን ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ተቀብለናል ሲሉም ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ሜጋ ፕሮጀክቶች ግንባታ የከተማዋ ገጽታ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሽ ሆናለች ያሉት ከንቲባዋ÷ ፕሮጀክት መጀመር ብቻ ሳይሆን በጊዜ ማጠናቀቅ የሚያስችል የስራና የአሰራር ባህል ተፈጥሯል በማለት ገልጸዋል።
በመዲናይቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች አለሁ የሚል አሳቢ አመራር መፈጠሩንም አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ከተሞች ከንቲባዎች ከዚህ ስኬት ልምድ ወስደው ከተሞቻቸውን የማላቅ እና የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና የሚያቃልሉ ሰው ተኮር ስራዎች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ ተስፋ አደርጋለሁ ብለዋል።
More Stories
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሪጅን በሚዛን ዲስትሪክት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ለማረጋገጥ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ
የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የህግ ትምህርት ቤቶች መካከል የተካሄደው 9ኛው የምስለ ችሎት ውድድር በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ አሸናፊነት ተጠናቀቀ