የመስቀል በዓል በዩኒስኮ እንደተመዘገበ ሁሉ በዳዉሮ የንጉስ ሃላላ የድንጋይ ኬላም ዕውቅና አግኝቶ እንዲመዘገብ ለማስቻል በተቀናጀ ጥረት ሊሠራ እንደሚገባ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ መስከረም 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የመስቀል በዓል በዩኒስኮ እንደተመዘገበ ሁሉ በዳዉሮ የንጉስ ሃላላ የድንጋይ ኬላም ዕውቅና አግኝቶ እንዲመዘገብ ለማስቻል በተቀናጀ ጥረት ሊሠራ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዳዉሮ እና ኮንታ አህጉረስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል አቡነ ጢሞቴዎስ ተናገሩ።
የንጉስ ሃላላ የድንጋይ ካብ እንዲመዘገብ እና ሌሎች የሕዝብ የቱሪዝም ሃብትና ቅርስ የሆኑት ተጠብቀው እንዲኖሩ ቤተክርስቲያኗ ከመንግሥት ጋር በጋራ ጉዳዮች ተባብራ እንደምትሰራም ነው የገለጹት።
በዕለቱ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይና የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳዊት ገበየሁ በበኩላቸው መስቀል የድልና የፍቅር መገለጫ በመሆኑ ድህነትን ለማሸነፍ የሚደረገውን ጥረት ምዕመናን በተሠማሩት የሥራ ዘርፍ ውጤታማ ተግባር እያከናወኑ፣ የተቸገሩትን በፍቅር ተገቢ እንክብካቤ በመስጠት ክርስቲያናዊ ግዴታቸውን መወጣት እንዳለባቸውም ገልጸዋል።
በዳዉሮ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊቀጳጳስ በመስቀል አደባባይ ተገኝተው ያከበሩበት በዓል ለከተማው ልዩ አጋጣሚ መሆኑን የተርጫ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዳዊት ወንድሙ ገልጸዋል።
ክርስቲያን ወገኖች በዓሉን ሲያከብሩ አንድነትን በማጠናከር፣ ለአካባቢያቸው ሰላም ዘብ መቆም እንዳለባቸውም ተገልጿል።
በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የተርጫ ከተማ ከንቲባ በህገ መንግሥቱ በተቀመጠው የአሠራር ሥርዓት በመታገዝ ለሕዝቡ ተጠቃሚነት ከሃይማኖት ተቋማት ጋር በአስተዳደራዊ፣ በማኅበራዊ፣ ኢኮኖያሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች በጋራ ለመሥራት ቁርጠኛ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ መሣይ መሠለ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
የፍትህ ተቋማት ተገልጋዩን ህብረተሰብ በሚመጥን መልኩ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ ገለፁ
በተገልጋይ እርካታና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፍትህ ትራንስፎርሜሽንና የፍርድ ቤቶች ጥምረት ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለጸ
የዜጎችን ህይወት በማቀራረብ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ከሚረዱ ጉዳዮች አንዱ የበጎ ፈቃድ ሥራ መሆኑ ተጠቆመ