በቡታጅራ ከተማ ቢሮዎች ዝግጁ ሆነዋል
ሀዋሳ: ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቡታጅራ ከተማ የተመደቡ ክላስተር መሥሪያ ቤቶች የቢሮ ዝግጅት መደረጉን የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ገለፁ::
ጳጉሜ 04 ቀን 2015 ዓ.ም የሥራ ማስጀመሪያ መርሀግብር እንደሚከናወንም ተገልጿል::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማዕከል ከተማ ከሆኑት አንዷ የሆነችው የቡታጅራ ከተማ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶችን ማጠናቀቋን የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ተናግረዋል::
ከደሬቴድ ጋር ቆይታ ያደረጉት ምክትል አስተዳዳሪው ከተማው የክላስተር ከተማ ሆና መመረጧ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል:: ይህም ከሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ከገበያ ትስስር እና ከኢንቨስትመንት አንፃር ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል ነው ያሉት::
ከተማዋ ለእንግዶች ምቹ ትሆን ዘንድ ከከተማ ፅዳት ጀምሮ እስከ ቢሮ ዝግጅት ያሉ ተግባራት መከናወናቸውን አስታውቀዋል:: ይህን ተከትሎ ጳጉሜ 04 ቀን 2015 ዓ.ም ከፍተኛ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ይፋዊ የሥራ ማስጀመሪያ መርሀግብር ይካሄዳል::
የቢሮ ኃላፊዎች በቀጥታ ወደ ሥራ በመግባት የተሰጣቸውን የህዝብና የመንግስታ ኃላፊነት ያለምንም ችግር ይወጡ ዘንድ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ሥራ መሠራቱን አቶ ሙስጠፋ ገልጸዋል::
ከከተማዋ ባለሀብቶች ጋር በመነጋገር ለኃላፊዎቹ ለ6 ወር በነፃ የሚኖሩበት የመኖሪያ ቤት ተዘጋጅቷል ብለዋል:: ባለሀብቱ ላሳየው በጎ ፈቃደኝነት ምስጋና አቅርበዋል::
ወደ ከተማዋ ተመድበው የሚመጡ የመንግስት ሠራተኞችም ባይተዋርነት ሳይሰማቸው እንደ ቤታቸው ሆነው እንዲኖሩ የሚያስችል ሥራ ከህብረተሰቡ ጋር ተሰርቷል ብለዋል::
እድገት በጊዜ ሂደት የሚመጣ መሆኑን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ለእንግዶች በተመጣጣኝ ዋጋ የመኖሪያ ቤት ማከራየት መልካም መሆኑን አንስተዋል::
በአራቱ ቢሮዎች ተመድበው ወደ ከተማዋ ለሚመጡ የመንግስት ሠራተኞች በማህበር በማደራጀት የመኖሪያ ቤት እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑም ቅድሚያ ተሰጥቶ እንደሚሠራ አብራርተዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር