በስልጤ ዞን ሚቶ ወረዳ 25 አዳዲስ ቤቶች እና 17 ያረጁ ቤቶች በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተገንብተው ለአቅመ ደካሞች እና ለመከላከያ ቤተሰቦች ተሰጡ
ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስልጤ ዞን ሚቶ ወረዳ 25 አዳዲስ ቤቶች እና 17 ያረጁ ቤቶች በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተገንብተው ለአቅመ ደካሞች እና ለመከላከያ ቤተሰቦች ተሰጥተዋል፡፡
በክረምቱ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች የተሰሩ የመንገድ፣ የአካባቢ ጥበቃና የተለያዩ የልማት ሥራዎች የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰባሀድን ሎባ ገልፀዋል፡፡
አስተያየት የሰጡ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍ ሁሉም ሰው በየአካባቢው የድርሻውን የሚወጡ ከሆነ የአገሪቱ ችግር በቀላሉ እንደሚቀረፍ ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ አበባ ሌንዲዶ

More Stories
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ
ዘመናዊ የግብርና ግብአት እና ቴክኖሎጂን በተገቢው በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የቀቤና ልዩ ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለፀ