በስልጤ ዞን ሚቶ ወረዳ 25 አዳዲስ ቤቶች እና 17 ያረጁ ቤቶች በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተገንብተው ለአቅመ ደካሞች እና ለመከላከያ ቤተሰቦች ተሰጡ
ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በስልጤ ዞን ሚቶ ወረዳ 25 አዳዲስ ቤቶች እና 17 ያረጁ ቤቶች በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተገንብተው ለአቅመ ደካሞች እና ለመከላከያ ቤተሰቦች ተሰጥተዋል፡፡
በክረምቱ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች የተሰሩ የመንገድ፣ የአካባቢ ጥበቃና የተለያዩ የልማት ሥራዎች የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰባሀድን ሎባ ገልፀዋል፡፡
አስተያየት የሰጡ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍ ሁሉም ሰው በየአካባቢው የድርሻውን የሚወጡ ከሆነ የአገሪቱ ችግር በቀላሉ እንደሚቀረፍ ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ አበባ ሌንዲዶ

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ